ለመጀመሪያ ጊዜ በ24 ሰዓት ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተደረገ

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-04-22

ሁለት አዳዲስ በቫይረሱ የተጠቁ ተገኝተዋል፤ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 21 ደርሷል፤ በአፋር ክልል በቫይረሱ የተጠቃ የመጀመሪያው ሰው ተገኘ

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 22, 2020)፦ እስካሁን በየዕለቱ በተደረጉ የላብራቶሪ ምርመራዎች ከአንድ ሺሕ በላይ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች ውስጥ ሁለት አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአክሱም ለይቶ ማቆያ ሊያመልጥ ሲል የተያዘ ግለሰብ የስድስት ወር እስራት ተፈረደበት

Axum

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 21, 2020)፦ በትግራይ ክልል በአክሱም ከተማ በለይቶ ማቆያ ማዕከል ውስጥ ገብቶ የነበረ አንድ ግለሰብ፤ ከለይቶ ማቆያው ሊያመልጥ ሲል መያዙንና የስድስት ወር እስራት እንደተፈረደበት ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግል ትምህርት ቤቶች ለሠራተኞቻቸው ያለ ቅድመ ሁኔታ ደምወዝ እንዲከፍሉ ተወሰነ

FDRE Ministry of Education

የተማሪዎች ክፍያ ከ50-70 በመቶው ብቻ ይከፈል ተብሏል

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 21, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ የትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሒደታቸውን ያቋረጡ ሲሆን፤ የግል ትምህርት ቤቶች ለሠራተኞቻቸው ከሚከፍሉት ደምወዝና ተማሪዎችን ክፍያ በተመለከተ ብዥታ ተፈጥሮ ቆይቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

21 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

በሐሰተኛ ሰነድና በቱሪስት ስም የገቡ ተሽከርካሪዎች

በሐሰተኛ ሰነድና በቱሪስት ስም የገቡ ተሽከርካሪዎች፣ 7,362 የመትረየስ፣ የክላሽና የቱርክ ሽጉጥ ጥይቶች ይገኙበታል

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 21, 2020)፦ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ። በሐሰተኛ ሰነድና በቱሪስት ስም የገቡ ተሽከርካሪዎች፣ 7,362 የመትረየስ፣ የክላሽና የቱርክ ሽጉጥ ጥይቶች ይገኙበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር መቶ ተሻገረ

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ጤና ሚኒስቴር

84ቱ በለይቶ ማቆያ ሕክምና ላይ ናቸው

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 18, 2020)፦ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው መረጃ፤ ባላፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደርገላቸው 659 ሰዎች፤ ዘጠኝ አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች በመገኝታቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 105 ደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 31ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 31st, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሠላሳ አንደኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከመጋቢት 28 - ሚያዝያ 4 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሥጋት ጋር በተያያዘ በመላው አገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጃለች። አዋጁ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 96 ደረሰ

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-04-17

ከአራቱ አዳዲስ በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ አንዱ ከዱባይ የመጣ ነው

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 17, 2020)፦ ባለፉት 24 ሰዓታት 842 ሰዎችን በመመርመር አራት አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች መገኘታቸውን በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተገኘባቸውን ሰዎች ቁጥር 96 አድርሶታል። ከአራቱ አዳዲስ በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ አንዱ ከዱባይ የመጣ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአሜሪካ 100 ኢትዮጵያውያን በኮሮና ቫይረስ መሞታቸውን ማረጋገጥ ተችሏል

Fitsum Arega, Ethiopian Ambassador to the United States

በአብዛኛው እየሞተ ያለው አፍሪካ አሜሪካውያን በሚል ካታጎሪ የተመደቡ ናቸው

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 17, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ በእጅጉ እየደቆሳት ባለችው አሜሪካ በተወሰነ ደረጃ ከተሰበሰቡ መረጃዎች 100 የሚኾኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በኮሮና ቫይረስ ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተመለከተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትራምፕ እንደዛቱት አደረጉት

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ (በግራ)፣ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም (በቀኝ)

ለዓለም ጤና ድርጅት የ400 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንዳይሠጥ አዘዙ

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 15, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ወረሽኝ ጋር በተያያዘ በዓለም ጤና ድርጅት ላይ ጥርሳቸውን የነከሱትና በአደባባይ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ሲወቅሱ የሰነበቱት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ አሜሪካ ለድርጅቱ ታደርግ የነበረውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታቋርጥ ትእዛዝ ሠጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ