ሐሰተኛ የብርና የዶላር ገንዘቦች ተያዙ

The new forged 100 birr notes

በሐሰተኛ መንገድ የተዘጋጁ 200 ሺህ የብር ኖቶችና 174 ሺህ 350 የነባሩ ብር ኖቶች ተይዘዋል
በሐሰት የተዘጋጀው ዶላር 14,800 ነው

ኢዛ (ዓርብ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 30, 2020)፦ የፌዴራል ፖሊስ የአዲሱንና የነባሩን (የአሮጌውን) ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች እና በተመሳሳይ መንገድ ሐሰተኛ የአሜሪካ ዶላሮችን መያዙን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ልደቱ የዋስትና ጥያቄ ላይ እና የክስ መቃወሚያ ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥጠ

Lidetu Ayalew

ከልባቸው ሕመም ጋር በተያያዘ የተገጠመላቸው ሰው ሠራሽ መሣሪያን በተመለከተ የሕክምና ቀጠሯቸው በማለፉ ለሕይወታቸው አስጊ መኾኑን ለፍርድ ቤቱ በደብዳቤ አሳውቀዋል

ኢዛ (ዓርብ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 30, 2020)፦ አቶ ልደቱ አያሌው ከተከሰሱበት ሁለተኛ መዝገብ ጋር በተያያዘ፤ ዛሬ ዓርብ ጥቅምት 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው በዚህ መዝገብ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ የተቀረጸው ድምፅ ግልባጭ ከመዝገቡ ጋር ባለመያያዙ፤ የክስ መቃወሚያና ዋስትናው ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለሰሜን ዕዝ አዲስ አዛዥ ተሾመ

ሜጀር ጄኔራል በላይ ስዩም

የሕወሓት ደጋፊዎች ዛቻዎች እየሰነዘሩ ናቸው

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፲፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 29, 2020)፦ የአገር መከላከያ ሚኒስቴር አራት የነበሩትን ዕዞች ወደ ስድስት በማሳደግ እንዲዋቀር ካደረገ በኋላ፤ መቀመጫውን መቀሌ ላደረገው የሰሜን ዕዝ አዲስ አዛዥ ተሾመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወጋገን ባንክ ፕሬዝዳንቱን አሰናበተ

Wegagen Bank

አዲሷ ፕሬዝዳንት በቅርቡ ሥራቸውን የጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 28, 2020)፦ የወጋገን ባንክ ፕሬዝዳንት ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ባስገቡት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ መሠረት፤ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቶ መሰናበታቸው ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የተቋረጠው የሦስትዮሽ ድርድር ዛሬ ይካሔዳል

PM Abiy Ahmed (L) and President Cyril Ramaphosa (R)

በድርድሩ ላይ የአፍሪካ ሕብረት ከሦስቱ አገራት መሪዎች ጋር መክሯል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 27, 2020)፦ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ በሦስቱ ተደራዳሪ አገራት ተቋርጦ የነበረው ድርድር ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ይካሔዳል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል ተወካዮች ላይ እርምጃ ሊወስድ ነው

Tafesse Chaffo is the Speaker of the Ethiopian House of Peoples Representatives

የደምወዝ እገዳና የተሰጣቸውን የመኖሪያ ቤት መቀማት ከእርምጃዎቹ ውስጥ ሊኾኑ እንደሚችሉ ተገምቷል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 21, 2020)፦ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በማይገኙ የትግራይ ክልል ተወካዮች (የምክር ቤት አባላት) አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወይዘሮ አዳነች አቤቤ ሹም ሽረት

Adanech Abebe

ሰባት የቢሮ ኃላፊዎች በአዲስ ተተክተዋል
ከአሥሩ ክፍለ ከተሞች ሥራ አሥፈጻሚዎች ሦስቱ ብቻ ቀርተዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 20, 2020)፦ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ እና ሌሎች ከፍተኛ የከተማው ቢሮ ኃላፊዎችን በአዲስ የተካ ሹመት ተሰጠ። ከአሥሩ የክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ሦስቱ ብቻ ባሉበት እንዲቀጥሉ ተደረገ። ሹመቱን የሰጡትና ያጸደቁት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ