ኢህአዴግ ካባረራቸው አባላቱ ጋር ለእርቅ እየተነጋገረ ነው

EPRDF ኢህአዴግ

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. June 7, 2015)፡- የትግል ታሪኩ ጥንካሬ በገዛ አባላቱ ተጋኖ የሚነገርለት ኢህአዴግ ሥልጣን ይዞ በቆየበት 24 ዓመታት ለህልውናው አስጊ የሆኑ ፈታኝ ጊዚያቶች በተደጋጋሚ አሳልፏል። ከእነዚህ ውስጥ በ1993 ዓ.ም. አመራሩ ለሁለት ተሰንጥቆ በነበረበት ጊዜ የደረሰው ውጣውረድ፣ በቀድሞው ጠ/ሚንስትር ሞት የደረሰው ክፍተት እንዲሁም የ1997ቱ ምርጫ ባስከተለው ህዝባዊ ዓመጽ መሬት ነክቶ የመመለሱ አደጋ የሚጠቀሱ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እረጭ ያለው ምርጫ

Ethiopian election 2015. እረጭ ያለው ምርጫበኢትዮጵያ የተካሄደውን የ2007ቱን ምርጫ አስመልክቶ የቪኦኤ ጋዜጠኛ ሰለሞን አባተ ባጠናከረው ዘገባ፣ "አዲስ አበባ ውስጥ ከባነሮቹና እጅግ ከተጋነነው የሙዚቃ ጩኸት በተረፈ አገሪቱ በ90 ሚሊዮን ሕዝብ የተመላች አትመስልም፤ ባልተለመደ ሁኔታ እረጭ ያለ ምርጫ" በማለት የምርጫውን ሁኔታ ገልጦታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሊቢያ በደቡብ አፍሪካና የመን ለተገደሉ ወገኖቻችን በሲድኒ የሻማ ማብራት ሥነሥርዓት ተከናወነ

አቢይ አፈወርቅ
Sydney candlelight vigil. በሊቢያ በደቡብ አፍሪካና የመን ለተገደሉ ወገኖቻችን በሲድኒ የሻማ ማብራት ሥነሥርዓት ተከናወነ

በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ያስቆጣቸው የሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን እሁድ ኤፕሪል 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ልዩ የሻማ ማብራት ስርአት አካሂደዋል። በዚህ በኒው ሳውዝ ዌልስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር አስተናባሪነት በተዘጋጀው ሥነሥርዓት ላይ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን ተገኝተው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሜልቦርን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ኢሰብዓዊ ጥቃት ተቃወሙ
Ethiopians protested in Meelbourne. በሜልበርን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ኢሰብዓዊ ጥቃት በመቃወም ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

ሚያዝያ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. (April 24, 2015) የሜልበርን ኢትዮጵያዊያን ኮሚኒቲ እና ዲሞክራሲ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ቡድን በሕብረት ባስተባበሩት የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር የነበረው ኢትዮጵያዊ ተሳትፎ ቁጣውን በመረረና እልህና ቁጭት በተንጸባረቀበት መልክ ሲገልጽ አርፍዷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእነብርሃኑ፣ ፍቅረማርምና እየሩሳሌም የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ

ኤልያስ ገብሩ

ተጨማሪ የ28 ቀናት ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል
‹‹ተጨማሪ ምርመራ ይቀረኛል›› መርማሪ ፖሊስ
‹‹መረጃዎች ካሉ ክስ ይመስረትብን ካልሆነ ከእስር እንለቀቅ›› ተጠርጣሪዎች

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የሚገኙት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ፣ ፍቅረማሪያም አስማማውና እየሩሳሌም ተስፋው ዛሬ ከሰዓት በኋላ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ፍርድ ችሎት ቀርበው ተጨማሪ የ28 ቀናት ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግሰለቦች የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ

ኤሊያስ ገብሩ

‹‹እኔ አሸባሪ አይደለሁም። ኢህአዴግ አሸባሪ ነው። ለሽብር ሀሳቡም ፍላጎቱም የለኝም›› ዳንኤል ሺበሺ

‹‹የተባለውን ለነገር አለማድረጌን ከእኔ በላይ የከሰሰኝ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል›› ሀብታሙ አያሌው

‹‹ለእኔ ብቸኛው አሸባሪ ህወሃት/ኢህአዴግ ነው። እኔ የህወሃት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ ነኝ›› አብርሃ ደስታ

‹‹ይሄ 19ኛ ችሎት የጦር ፍርድ ቤት ችሎት እየመሰለ ነው›› የሺዋስ አሰፋ

‹‹ኃይማኖቱንና ማኅበረሰቡን ከሚፈራ ህዝብ ወጥቼ እንዲህ አይነት ተግባር አልፈጽምም›› ባህሩ ታዬ

ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2007 ዓ.ም፣ በከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙት እና በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ያሉ 10 ሰዎች ቀርበው ነበር። መዝገቡ ለዛሬ የተቀጠረው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ለመቀበል እና ከ1-5ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተከሳሾች በእስር ቤቱ ደረሰብን ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ላይ አስተያየት ካላቸው ለመቀበል መሆኑን የችሎቱ የግራ ዳኛ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” (ሂዩማን ራይት ዎች)

በኢትዮጵያ የመገናኛ-ብዙሃን ነጻነት ላይ የሚፈፀም የመብት ጥሰት እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 2015 ዓ.ም.

ማጠቃለያ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) እ.ኤ.አ. በ2010 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ 99.6 በመቶ የፓርላማ መቀመጫን ካሸነፈ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሃሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና መረጃ የማግኘት መብትን በመገደብ በግል መገናኛ-ብዙሃን ላይ እያሳደረ ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ አባብሶታል። እ.ኤ.አ. ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ ቢያንስ 60 ጋዜጠኞች ሃገር ለቀው የተሰደዱ ሲሆን ሌሎች 19 ጋዜጠኞች ደግሞ በእስር ላይ እየተሰቃዩ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእምነት ክህደት ቃል በኃይል አስፈርመዋቸዋል

መዝገቦቹ መልሰው ተቀራረቡ

ጽዮን ግርማ

የሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን የሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. የፍርድ ቤት ቀጠሮ

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በስድስቱ ጦማሪያንና በሦስቱን ጋዜጠኞች ላይ የፌደራል ፖሊስ የተለያየ ምክንያት እየሰጠ ቀጠሮ የሚያራዝመውን ሁለት መዝገብ አንዴ ሲያቀራርበው መልሶ ደግሞ ሲያራርቀው ቆይቶ አሁን ደግሞ መዝገቦቹን መልሶ አቀራርቧቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወጣቶቹና - ቅዳሜ

አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት
በዛሬው ችሎት ፖሊስ የሃያ ስምንት ቀን የምርምራ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደለት

ጽዮን ግርማ

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፉ ብርሃነ Journalist Tesfalem Weldeyes, Zelalem Kibret, journalist Asmamaw H/ghiorgis, journalist Edom Kassaye, Natnael Feleke and Atnaf Berhane

ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ”ቅዳሜ” ትርጉም አላት። የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ”ቅዳሜ”ን ደግሞ እንደየምድቡ ይውልባታል። እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት። ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ