ተጨማሪ ስድስት ሰዎች ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ

ኮሮና ቫይረስ

በቫይረሱ የተያዙት ቁጥር 35 ደረሰ

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 3, 2020)፦ ዛሬ መጋቢት 25 ቀን ጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው ከኾነ፤ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 74 ሰዎች ውስጥ ስድስቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙትን ቁጥር 35 አድርሶታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 29ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 29th, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሃያ ዘጠነኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከየካቲት መጋቢት 14 - 20 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ እንደቀደሙት ሳምንታት ሁሉ ባሳለፍነውም ሳምንት በአገር ቤትም ኾነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኮሮናን የተመለከቱ ዜናዎችን የሚያስተካክል አልነበረም። አሁንም ይህ የዓለም ውጋት የኾነው ወረርሽኝን የተመለከቱ ዜናዎችን የሚስተካከል አልነበረም። አሁንም ይህ የዓለም ሕመምና ውጋት የኾነው ወረርሽኝን የተመለከቱ ዜናዎች በደቂቃዎች ልዩነት ሰዎች እንደዋዛ የሚረግፉበት ኾኖ ቀጥሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ ሦስት ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ

3ዲ (3D) ኮሮና ቫይረስ በምስል (© istock.com/Dr_Microbe)

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ቁጥር 29 ደረሰ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 1, 2020)፦ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደገለጸው ከኾነ፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከመረመራቸው 68 ሰዎች ውስጥ ሦስቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አረጋግጧል። ይህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙትን ቁጥር 29 አድርሶታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከኮሮና ወረርሽኝ ዙሪያ ምክረ ሐሳብ አቀረበ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን

ክልሎች ድንበራቸውን መዝጋት ብቸኛ መፍትሔ አይደለም

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የክልል መንግሥታት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በክልሎች መካከል ያለውን ድንበር መዝጋት ሳይሆን በመግቢያ ድንበሮች ምርመራ ማድረግ ሊሆን እንደሚገባ ዛሬ መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. በምክረ ሐሳብ ደረጃ ይፋ ባደረገው መልእክቱ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች 7 ሺህ 650 ታራሚዎች እንዲለቀቁ ተወሰነ

የአማራ ብሔራዊ ክልል መስተዳድር ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ

123ቱ ሴቶች ናቸው

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የአማራ ክልላዊ መንግሥት 7 ሺህ 650 ለሚኾኑ የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ በማድረግ ከእስር እንዲፈቱ ወሰነ። የክልሉ መንግሥት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል እንደኾነ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሼህ መሐመድ አል-አሙዲን ለአዲስ አበባ 120 ሚሊዮን ብር ሠጡ

Sheikh Mohammed Hussein Al Amoudi

የሜድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ደግሞ 20 ሚሊዮን ብር ለአገር አቀፉ ኮሚቴ ድጋፍ ሠጥቷል

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚያስፈልገው ፋይናንስ ሼህ መሐመድ ሑሴን አል-አሙዲ የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኮሮና ወረርሽኝ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥጋትና ተማፅኖ

PM Abiy Ahmed

ክልሎች የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቋረጥ እየወሰኑ ነው
የፓርቲና ሌሎች ስብሰባዎች ክልከላ ተጥሏል
በአማራ ክልል ዛሬ በተገኙት በቫይረሱ ከተጠቁ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው 24 ሰዎች
ወደ ክልሎች የሚገቡ ሰዎች ሪፖርት የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል
በጡረታ የተገለሉ የጤና ባለሙያዎችና የጤና ተማሪዎች ለግዳጅ ተዘጋጁ ተብሏል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 30, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 23 ስለመድረሱ ሲገለጽ ይህ መረጃ እንደ ቀድሞዎቹ ተመሳሳይ ሪፖርቶች በጤና ሚኒስትርና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል የተነገረ አልነበረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በናዝሬት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጧል

አዳማ / ናዝሬት

የሰዎች እንቅስቃሴዎች ተገድበዋል

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 29, 2020)፦ ሰሞኑን በአዳማ (ናዝሬት) የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ሰው መኖሩ ሪፖርት ከተደረገ በኋላ፤ በአዳማ እንቅስቃሴዎች እየተቀዛቀዙ መጥተው ዛሬ ሙሉ ለሙሉ የትራንስፖርትና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ቆመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ