በኢትዮጵያ የቫይረሱ ተጠቂዎች 38 ደረሱ
የ85 ዓመቷ አዛውንት አገግመዋል
ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 4, 2020)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 38 መደረሱን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የ85 ዓመቷ አዛውንት ማገገማቸው ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 4, 2020)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 38 መደረሱን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የ85 ዓመቷ አዛውንት ማገገማቸው ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 3, 2020)፦ ዛሬ መጋቢት 25 ቀን ጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው ከኾነ፤ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 74 ሰዎች ውስጥ ስድስቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙትን ቁጥር 35 አድርሶታል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ከየካቲት መጋቢት 14 - 20 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ እንደቀደሙት ሳምንታት ሁሉ ባሳለፍነውም ሳምንት በአገር ቤትም ኾነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኮሮናን የተመለከቱ ዜናዎችን የሚያስተካክል አልነበረም። አሁንም ይህ የዓለም ውጋት የኾነው ወረርሽኝን የተመለከቱ ዜናዎችን የሚስተካከል አልነበረም። አሁንም ይህ የዓለም ሕመምና ውጋት የኾነው ወረርሽኝን የተመለከቱ ዜናዎች በደቂቃዎች ልዩነት ሰዎች እንደዋዛ የሚረግፉበት ኾኖ ቀጥሏል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 1, 2020)፦ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደገለጸው ከኾነ፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከመረመራቸው 68 ሰዎች ውስጥ ሦስቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አረጋግጧል። ይህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙትን ቁጥር 29 አድርሶታል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የክልል መንግሥታት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በክልሎች መካከል ያለውን ድንበር መዝጋት ሳይሆን በመግቢያ ድንበሮች ምርመራ ማድረግ ሊሆን እንደሚገባ ዛሬ መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. በምክረ ሐሳብ ደረጃ ይፋ ባደረገው መልእክቱ አስታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የአማራ ክልላዊ መንግሥት 7 ሺህ 650 ለሚኾኑ የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ በማድረግ ከእስር እንዲፈቱ ወሰነ። የክልሉ መንግሥት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል እንደኾነ ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚያስፈልገው ፋይናንስ ሼህ መሐመድ ሑሴን አል-አሙዲ የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 31, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አገራዊ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ማካሔድ እንደማይችል አስታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 30, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 23 ስለመድረሱ ሲገለጽ ይህ መረጃ እንደ ቀድሞዎቹ ተመሳሳይ ሪፖርቶች በጤና ሚኒስትርና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል የተነገረ አልነበረም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 29, 2020)፦ ሰሞኑን በአዳማ (ናዝሬት) የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ሰው መኖሩ ሪፖርት ከተደረገ በኋላ፤ በአዳማ እንቅስቃሴዎች እየተቀዛቀዙ መጥተው ዛሬ ሙሉ ለሙሉ የትራንስፖርትና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ቆመዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...