ቢቢሲ በሦስት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ስርጭት ሊጀምር ነው

BBC

ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ የብሪቲሽ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ቢቢሲ)፣ በሚቀጥለው የአውሮፓውያን አዲስ ዓመት (2017) የኢትዮጵያን ሦስት ቋንቋዎች ጨምሮ በአስራ አንድ የዓለም ቋንቋዎች አዲስ ስርጭት ሊጀምር መሆኑ ታወቀ። ኢትዮጵያውያን ቋንቋዎቹ አማርኛ፣ ኦሮምኛ እና ትግሪኛ መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ የአንድ ዓመት እስራት ተፈረደበት

Journalist Getachew Workuኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 15, 2016)፦ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ፮ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በዋለው ችሎት፤ በኢትዮ ምኅዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ላይ የአንድ ዓመት እስራት እንደበየነበት ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ ጠቆመ። ጋዜጠኛ ጌታቸው ካለፈው ጥቅምት ፳፬ ቀን ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ ሃያ ሁለት ሰዎች በሽብርተኝነት ክስ ተመሰረተባቸው

Oromo protest

ኢትዮጵያ ዛሬ (ሰኞ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 14, 2016)፦ አቃቤ ሕግ፤ ከኦነግ አመራሮች ተልዕኮ በመቀበል በምዕራብ ወለጋ ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ኹከት ፈጥረዋል ባላቸው ፳፪ (22) ሰዎች ላይ በሽብርተኝነት ዛሬ ክስ መመስረቱን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ አስረዳ። ክሱ የተመሰረተው አዲስ አበባ በሚገኘው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፬ኛ ወንጀል ችሎት መሆኑ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሀብታሙ አያሌውን ጨምሮ አራት ታዋቂ ፖለቲከኞች ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

Habtamu, Daniel, Yeshiwas and Abraha

ኢትዮጵያ ዛሬ (ሰኞ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 14, 2016):- አራት ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎች፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በነገው ዕለት በፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ ጠቆም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እሳተ ገሞራ በዝርይ ተራራ ሊፈነዳ ይችላል ተበሎ እየተጠበቀ ነው

Volcanic eruption on Zeriy mountain around Injibara

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. November 12, 2016):- በእንጅባራ ከተማ በስተሰሜን ፭ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውና እንደዋ ቀበሌ ውስጥ ያለው ዝርይ የተባለው ፬፻ ሜትር ከፍታ እንዳለው የሚገመተው ተራራ፤ ከትናንት ኅዳር ፪ ቀን ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ጀምሮ መጨስ መጀመሩንና ምክንያቱ እሳተ ገሞራ እንደሆነ ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች ጠቆሙ። እሳተ ገሞራው ከፈነዳ አካባቢው በውሃ ሊጥለቀለቅ ይችላል የሚል ፍራቻ አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲሱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኃይሌ ገብረሥላሴ የዕድሜ ልክ ክብር ተጎናጸፈ

Haile Geberselase

ኢትዮጵያ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. November 11, 2016):- የዓለም አቀፉ የማራቶንና የረዥም ርቀት ማኅበር በዛሬው ዕለት ከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ኹኖ የተመረጠውን አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴን የዕድሜ ልክ ሽልማት ወደር የማይገኝለት የማራቶን ሯጭ የሚል የክብር ስያሜ በመስጠት ለክብሩ የራት ግብዥ የማራቶን ውልድት ከተማ በሆነችው የግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ አዘጋጅቶለታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ አቶ በቀለ ገርባ ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ

Bekele Gerba and others- መቅረብ ከነበረባቸው 22 ሰዎች አምስቱ አልቀረቡም

- "አራቱ የተለያየ እስር ቤት ስለሆኑ አላቀረብኳቸውም አንዱ ግን የት እንዳለ አላውቅም" ፖሊስ

ከቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት በአቃቤ ሕግ በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አመራር አባላትና ደጋፊዎች መካከል አምስቱ ዛሬ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ ሲል የአሜሪካ ድምፅ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኮማንድ ፖስቱ በመላ አገሪቱ 11 ሺህ 607 አስሬያለሁ እያለ ነው

"የታመኑት 11 ሺህ 607 ከሆኑ ያልታመኑት ስንት ሊሆኑ ነው" አስተያየት ሰጪዎች

Ethiopian protesters

Ethiopia Zare (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. November 11, 2016):- ኮማንድ ፖስቱ 11 ሺህ 607 ሰዎችን በመላው አገሪቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማሰሩን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ መግለጹን ፋና ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዞን ዘጠኝ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ በድጋሚ ታሰረ

Zone9 blogger Befeqadu Hailu(ዞን ዘጠኝ) የዞን ዘጠኝ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም./ Nov. 11, 2016) ማለዳ 12:30 ሰዓት ገደማ ኮማንድ ፓስት ይፈልግሃል በሚል ሰበብ ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ፤ እዛው መኖሪያ ቤቱ አካባቢ በሚገኝው 06 ፖሊስ ጣቢያ ታስሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ