ኮማንድ ፖስቱ ትናንት ሁለት ተጨማሪ ጋዜጠኞቸን አሰረ

Elias, Anania, and Daniel

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ኅዳር ፲ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 19, 2016)፦ የአዲስ ጉዳይ መጽሔት አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አናንያ ሶሪ ትናንት አርብ ኅዳር ፱ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. ኮማንድ ፖስቱ ማሰሩን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ አስረዳ። ጋዜጠኞቹ የታሰሩት በማኅበራዊ ድረገጾች ላይ በመሳተፋቸው መሆኑን ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ኢህአዴግን ውይይት በማዘግየት ከሰሡ

Prof. Beyene and PM. Hailemariam

(ቪኦኤ፣ ኅዳር ፲፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም./ኖቨምበር ፲፯ ቀን ፳፻፲፮ እ.ኤ.አ.) ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር ጋር መሠረታዊ በሆኑ ፖለቲካዊ ችግሮች ላይ ለመነጋገር መወያየታቸው ተነገረ፤ እስካሁን ግን ከገዢው ግንባር ተጨባጭ እርምጃ እንዳልተወሰደ የመድረክ መሪ አስታውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በአስቸኳይ እንዲፈታ ተጠየቀ

Zone 9 bloggers

ኢትዮጵያ ዛሬ (ኀሙስ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 17, 2016)፦ በምህጻረ ቃል ሲፒጄ በሚባል የሚታወቀው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ዛሬ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የመንግሥትን አያያዝ የተቹ ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸውን አስታውሶ "በአስቸኳይ እንዲፈቱ" ሲል በአጽንኦት ጠይቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዮናታን ተስፋዬ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት እንደሚታሰር ተዘገበ

Ato Yonatan Tesfaye(ኢሰመፕ) ፌስቡክ ላይ በጻፋቸው ጹሁፎች ምክንያት የሽብር ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍ/ቤት እየታየ የሚገኘውና በእስር ቂሊንጦ ያለው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ከአርብ ኅዳር 2/2009 ዓ.ም. ጀምሮ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድ አባት ሦስት ልጆች እንደተገደለባቸው ገለፁ

“እኔ ገጠር ተቀምጬ ልጆቼን ከተማ ነበር የማኖራቸው። በታጣቂዎች መገደላቸውን ሰምቼ ወደ ሚኖሩበት ከተማ ስሄድ የሦስቱንም ወንድ ልጆቼን አስከሬን ደጄ ላይ ወድቆ አገኘሁት” - አቶ ጀማል ሁሴን ለአሜሪካ ድምፅ

Killing in Oromia

(ቪኦኤ፣ ኖቨምበር ፲፮ ቀን ፳፻፲፮ እ.ኤ.አ.) በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በምስራቅ አርሲ ዞን ውስጥ በሽርካ ወረዳ ነዋሪ የሆኑ አቶ ጀማል ሁሴን የተባሉ ግለሰብ ሦስት ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደተገደሉባቸው ለአሜሪካ ድምጽ አፋን ኦሮሞ ዝግጅት ክፍል ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ባለፉት ፵፭ ቀናት ከ፲፫ እስከ ፴፱ ሚሊዮን ዶላር አጥታለች

Ethiopia blocked Facebook, Whatsup, Viber, internet

ኢትዮጵያ ዛሬ (ኀሙስ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 17, 2016)፦ ዛሬ ኢትዮጵያ ኢንተርኔት ከዘጋች አርባ አምስተኛ ቀን ሆናት። ላለፉት አርባ አምስት ቀናት አገሪቱ ኢንተርኔት በመዝጋትዋ ቢያንስ ፲፫ (13) ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንዳጣች የኢትዮጵያ ዛሬ የዜና ዝግጅት ክፍል ”ሴንተር ቴክኖሎጂ ኢኖቬሽን” ከዚህ በፊት ያወጣውን መረጃ መሰረት በማድረግ ያሰላው ስሌት ጠቆመ። ስሌቱ ያላካተታቸው መስፈርቶች ቢካተቱ ኪሳራው ወደ ፴፱ (39) ሚሊዮን ዶላር ሊጠጋ ይችላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት ነጻነት በዓለም ከመጨረሻዎቹ አራተኛ ሆነች

Freedom house internet freedom index

ኢትዮጵያ ዛሬ (ኀሙስ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 17, 2016)፦ ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በማግኘት ነጻነት ከዓለም አገራት ከመጨረሻዎቹ በአራተኝነት ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ”ፍሪደም ኃውስ” የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ያወጣው ዓመታዊ ሰነድ መጠቆሙን ኳርትዝ አፍሪካ ዘገበ። ከአፍሪካ የመጨረሻዋ አገር እንደሆነች ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነአቶ ሀብታሙ አያሌው ጉዳይ በድጋሚ ለኅዳር ፳፯ ተቀጠረ

Habtamu, Daniel, Yeshiwas and Abrahaኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ በአራት ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎች፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ አቶ አብርሃ ደስታ እና የፓርቲ አባል ባልሆኑት አቶ አብርሃም ሰለሞን የተከሰሱበትን ጉዳይ ለማየት የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ትናንት ቢሰየምም፤ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ በችሎቱ ባለመገኘቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእነበቀለ ገርባ ላይ የፌዴራል አቃቤ ሕግ በዝግ ችሎት ይታይልኝ ጥያቄን ፍ/ቤቱ ውድቅ አደረገው

Ene Bekele Gerbaኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ ዛሬ በዋለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፲፰ኛ ወንጀል ችሎት፣ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ ትናንት የእነ አቶ በቀለ ገርባ ጉዳይ ላይ ምስክርነት የመስጠቱ ሂደት በዝግ ችሎት እንዲታይለት ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አደረገበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ አበባ ውስጥ ሴት የፓርላማ አባል ተገደሉ

Ms. Addisie Zelekeመንግሥት በተፈጥሮ ነው የሞቱት ቢልም፤ ሳይገደሉ እንዳልቀሩ ይጠረጠራል

ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ የተከበሩ የፓርላማ ተመራጭ ወ/ሮ አዲሴ ዘለቀ አዲስ አበባ በሚገኘው ጽሕፈት ቤታቸው ትናንት ተገድለው እንደተገኙና ዛሬ እንደተቀበሩ ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ አስረዳ። የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ”ባጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም” ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን ቢዘግቡም፤ ወ/ሮ መገደላቸውን የሚጠቁሙ ያልተጣሩ ፍንጮች እንዳሉ ከደረሰን ዘገባ ለመረዳት ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ