የኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ ወዳጅ ፊደል ካስትሮ አረፉ

Fidel Castro

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ኅዳር ፲፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 26, 2016)፦ የቀድሞው የኩባ ፕሬዝዳንት ፊደል ካስትሮ በዘጠና ዓመታቸው ትናንት ማረፋቸው ተሰማ። ፊደል ካስትሮ ኩባን ለ፵፱ (49) ዓመታት ከመምራታቸውም ባሻገር በአብዮተኝነታቸውና በታጋይነታቸው በዓለም ላይ ታዋቂ የነበሩ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ወዳጅና ረዳት እንደነበሩም ይታወሳል። ኩባ የቀድሞ ፕሬዝዳንትዋን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክታ ለዘጠኝ ቀናት ብሔራዊ የኀዘን ቀን አውጃለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ መንግሥት በቁጥጥር ስር ያዋላቸውን አብራሪዎች ለቀቀ

The vintage planes had taken off from Sudan for the three-hour flight into Ethiopia

ኢትዮጵያ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፲፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 25, 2016)፦ ትናንት የአየር ንብረቴን በሕገ ወጥ መንገድ ሲያቋርጡ ያዝኳቸው ያላቸውን 20 ቀላል አውሮፕላኖችንና በውስጡ የሚገኙ 42 የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የተናገረው መንግሥት አሁን እንደለቀቃቸው ይፋ አድርጓል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!" ፕ/ር መረራ ጉዲና

የቀድሞ ተማሪያቸውና የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ወርቅነህ ገበየሁ የአያት ስም ”ነገዎ” ሳይሆን ”ወልደኪዳን” እንደሆነ መሰከሩ

Prof Merera Gudina meeting with Ethiopian in Amsterdam, 20th Nov. 2016

"በውይይት የማይፈታ ችግር የለም። ስትወያዩ ግን የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱ ላይ አታተኩሩ። ትኩረታችሁን አሁን የተጋፈጥናቸው ችግሮች ላይ አድርጉ።" ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢሳት መርጃ የገንዘብ ማሰባሰብ ተደረገ

ESAT fundraising, Stockholm Nov. 19, 2016

ኢትዮጵያ ዛሬ (እሁድ ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 20, 2016)፦ በስዊድን ርዕሰ ከተማ ስቶክሆልም ለኢሳት መርጃ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ተደረገ። ዝግጅቱን ያስተባበረው የስዊድን የኢሳት ድጋፍ ኮሚቴ ሲሆን፣ በዝግጀቱ ላይ በእንግድነት ጋዜጠኛ መሳይ መኮንንና ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀፀላ ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታላቁ ሩጫ ከአራት ዓመታት በኋላ ወደ መስቀል አደባባይ ተመለሰ

The great Ethiopian run

ኢትዮጵያ ዛሬ (እሁድ ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 20, 2016)፦ አንዴ በጸጥታ ችግር ሌላ ጊዜ በመንገድ ስራ ተሳቦ ላለፉት አራት ዓመታት ከህዝባዊው አደባባይ ርቆ የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሩጫ ዛሬ ወደ መስቀል አደባባይ ተመልሶ ተከናውኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሹም ሽሩ ሥልጣናቸውን ያጡ የኢህአዴግ ጎምቱ ባለሥልጣናት የሙሉ አምባሳደርነት ሹመት ተሰጣቸው

ከ፲፯ (17) ቀን በኋላ አዲስ ሥልጣን ተሰጣቸው

Ato Tsegaye Berhe, Ato Redwan Hussen, W/o Zenebu Tadesse, and Ato Tolossa Shagie

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ኅዳር ፲ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 19, 2016)፦ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ባለፈው ሹም ሽር ሥልጣናቸውን ላጡ ስምንት የኢህአዴግ የቀድሞ ባለሥልጣናት የሙሉ አምባሳደርነት ሹመት ሰጡ። እነኝህ የኢህአዴግ ጎምቱ ባለሥልጣናት የሙሉ አምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ቢገልጽም፤ በየትኞቹ አገሮች ላይ ሹመት እንደተሰጣቸው አልገለጸም፤ ተሰናባቾቹ አምባሳደሮችም አልታወቁም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊቷ በኮንትሮባንድ ሦስት ኪሎ ወርቅ ለሁለተኛ ጊዜ ሕንድ ይዛ ስትገባ ተያዘች

Indira Gandhi international airport arrivals

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ኅዳር ፲ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 19, 2016)፦ አንዲት ኢትዮጵያዊት ስምንት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ሩፒስ (የሕንድ ገንዘብ) የሚያውጣ ሦስት ኪሎ ወርቅ ይዛ በኢንድራ ጋንዲ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በኩል ስትገባ የሕንድ ጉምሩክ ባለሥልጣን በቁጥጥር ስር አዋላት። ኢትዮጵያዊቷ በእጅዋ ላይ አስር ሺህ የአሜሪካ ዶላር እና ስድሳ ሺህ ሩፒስ ተይዞባታል። ግለሰብዋ በወርቅ ኮንትሮባንድ በሕንድ ፖሊስ ስትያዝ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ