14 የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ታገዱ

የኢፌ.ዲ.ሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

አብዛኞቹ በቀድሞ የሕወሓት መኮንኖች የተቋቋሙ ነበሩ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የጁንታው የሕወሓት ቡድን ተልዕኮ በማስፈጸም ተደርሶባቸዋል የተባሉና ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ ሲሠሩ የተደረሰባቸውን 14 የግል የጥበቃ ኤጀንሲዎችን ማገዱን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰሜን ዕዝ የራዲዮ መገናኛ በመጥለፍ የተጠረጠሩ ከፍተኛ መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ)

በአገር ክህደት ጭምር ይጠየቃሉ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የሰሜን ዕዝን የራዲዮ መገናኛ በመጥለፍ የተጠረጠሩት የመከላከያ ኮምዩኒኬሽን ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱን ጨምሮ ሰባት ጄኔራሎች አገርን በመክዳት ወንጀልና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ በማሰብ ወንጀል ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ጁንታውን የሚቃወሙ ሰልፎች ተካሔዱ

በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ጁንታውን በመቃወም ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም. የተካሔዱ ሰልፎች

መንግሥት ሕግ የማስከበሩን ሥራ አጠንክሮ እንዲቀጥል ማሳሰቢያ ተሰጠ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በቅርቡ በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት የሚቃወሙ ሰልፎች ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በተለያዩ የክልል ከተሞች ተካሒደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለአገር መከላከያ የሚሰጠው ድጋፍ ቀጥሏል

Muferiat Kamil

ድጋፉን በማዕከል ለማድረግ ኮሚቴ ተዋቅሯል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ለመከላከያ ሠራዊት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ለማስተናገድ የተለያዩ የፌደራል ተቋማትን ያሳተፈ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋሙንና የመከላከያ ሠራዊት እያካሔደ ያለውን ሕግን የማስከበር ሥራ በመደገፍ ሕብረተሰቡ ፍቅርና ክብሩን እየገለጸ እንደሚገኝ የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህንን የገለጹት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነፃ በወጡ የትግራይ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደር እንደሚቋቋም ተገለጸ

Kenea Yadeta, defence minister

ሕወሓት በአምስት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሠራጨ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ከጥፋት ኃይሉ ነፃ በወጡ የትግራይ ክልል አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደር የሚቋቋምለቸው መኾኑን የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር ቀነአ ያደታ ዛሬ ረቡዕ ኅዳር 2 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ አስታወቁ። ቡድኑ በአምስት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሠራጨ መኾኑንም ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አዲስ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሾመ

አቶ አብርሃም አለኸኝ እና አቶ አገኘው ተሻገር

አቶ አብርሃም አለኸኝ አዲሱ ተሿሚ ኾነዋል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ አገኘው ተሻገር የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኾነው መሾማቸውን ተከትሎ፤ የክልሉን የብልጽግና ጽሕፈት ቤት እንዲመሩ አቶ አብርሃም አለኸኝ ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በታሪኳ እንደ ሕወሓት ዐይነት አረመኔ ገጥሟት እንደማያውቅ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ

Demeke Mekonen

ከሃዲ ቡድኑ ማንነት ላይ ያነጣጠረውን ጥቃት ቀጥሏል አሉ

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ዛሬ በይፋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሥራቸውን የጀመሩት አቶ ደመቀ መኮንን በምድር ላይ የመጨረሻ የክፋት መገለጫዎችን ከመፈጸም ወደኋላ የማይመለሰው ቡድን፤ በየክልሉ ጽንፈኞችን እያስተባበረ በማንነት ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ መፈጸሙን ቀጥሎበታል አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰሜን ዕዝን መገናኛ በመቁረጥ ሠራዊቱን በማስጨፍጨፍ የተጠረጠረው ጄኔራል ተያዘ

ሜጀር ጄኔራል ገብረመድኅን ፍቃዱ (ወዲ ነጮ)

ከጄኔራሉ በተጨማሪ 16 ተባባሪ ግብረአበሮቹም ተይዘዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 10, 2020)፦ በሰሜን ኢትዮጵያ መቀሌ የሚገኘውን የሰሜን ዕዝ ከማዕከል ጋር እንዳይገናኝና የመገናኛ ሥርዓቱ እንዲቋረጥ በማድረግ፤ በጁንታው የሕወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈጽም ሲያመቻቹ የነበሩ ጄኔራል መኮንኖች በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ጁንታው የሕወሓት ቡድን ሬሳችንንም ጭምር ነው ጅብ ያስበላው” ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ

L. Gen. Bacha Debele

ድርጊቱን የፈጸሙትና የጁንታው ተባባሪዎች የሠራዊቱ አባላት፣ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻዎች እና የኦነግ ሸኔ ናቸው

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 10, 2020)፦ በመቀሌ የመሸገው የሕወሓት ጁንታ ቡድን በሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ የፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት፤ የተሰዉ የአገር መከላከያ ሠራዊትን አስከሬን አውሬ እስከማስበላት የደረሰ ዘግናኝ ተግባር የተፈጸመበት ጭምር እንደነበር ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትውልደ ኢትዮጵያውያኖቹ በአሜሪካ ምርጫ ቀንቷቸዋል

Samra Brouk and Alexander Assefa

በኔቫዳና በኒው ዮርክ ሪፐብሊካንን አሸንፈዋል
ሳምራ ብሩክ በኒው ዮርክ የመጀመሪያዋ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴናተር ኾናለች

ኢዛ (ቅዳሜ ጥቅምት ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 7, 2020)፦ በአሜሪካ የዴሞክራት ፓርቲን ወክለው በሁለት የአሜሪካ ግዛቶች ለምርክ ቤት አባልነት እጩ ኾነው በመቅረብ የሪፐብሊካን ተፎካካሪዎቻቸውን አሸንፈዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ