ወለላዬ ከስዊድን

(ግጥሙን በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)

ዘመን ፊትሽ ተከምሮ

ለአርቲስት ሰብለ ተፈራ / Artist Seble Tefera

እየታየ ሥራሽ አምሮ

እንቁጣጣሽ አንድ ብለሽ

አርባ ድረስ ዕድሜ ቆጥረሽ

እንደ ቤቶች የሳቅ ተውኔት

እንደ ጨቤ ስካር ሕይወት

ሞት ራሱን ያሾፍሽበት

ለምንድነው? በይ ንገሪኝ

እባክሽን አደብቂኝ

 

ባንቺው ቀዬ የተወለድኩ

ፊደል በጄ እዛው የያዝኩ

መስፍን ሜዳ የተራገጥኩ

በጨበጣ ብይ ያስቆጠርኩ

ቲቸር ታዬ ያስተማሩኝ

ገብሬ ኩርኩም ያቀመሰኝ

የሲሚንቶ ጭስ ያወዛኝ

ቅዱስ ያሬድ ተሳልሜ

ከሽፋ ቤት ተሰይሜ

ያቶ ማሞን ኪኒን ቅሜ

እዛው ኖሬ እዛው ያደኩ

የቃጠሎው ቀን የተረፍኩ

እኔ እማውቅሽ የማታውቂኝ

የሰፈርሽ አንድ ሰው ነኝ

 

ይሄን ሁሉ ዘርዝሬልሽ

ጥያቄዬን ስጠይቅሽ

ዝም አትይም መቼም ከፍተሽ

ፊት ለፊትሽ ተስፋሽ ሞልቶ

እየታየ ዝናሽ ጎልቶ

እንደጸደይ ባገር ፈክተሽ

በህዝብ ፊት ደምቀሽ ታይተሽ

በአዲስ ዓመት በንቁጣጣሽ

በዕለቱ ለት ምን ቀጠፈሽ?

 


መታሰቢያነቱ ለአርቲስት ሰብለ ተፈራ ይሁንልኝ!

 

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ