አቶ ለማ መገርሳ በመከላከያ ጉዳይ ለመምከር ዋሽንግተን ዲሲ ናቸው

Lemma Megersa

ምክክሩ በኢትዮጵያና በአሜሪካን የሁለትዮሽ የመከላከያ ትብብር ለማጠናከር እንደኾነ ተደምጧል

ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 2, 2019)፦ ከሰሞኑ አነጋጋሪ የኾነ ቃለምልልስ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የሠጡት የመከላከያ ሚኒስትርና የኦዴፓ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ የመሩት የልዑካን ቡድን ዋሽንግተን ዲሲ መግባቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብልጽግና መሪዎች ፊርማቸውን አኖሩ

ሦስቱ የኢሕአዴግ እኅት ድርጅቶችና የአምስቱ አጋር ድርጅቶች ሊቃነመናብርት ፊርማቸውን ሲያኖሩ

ከሕወሓት በስተቀር በኢሕአዴግ ጥላ ሥር የነበሩት ስምንት ፓርቲዎች ውሕደቱን ፈጽመዋል

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 1, 2019)፦ የኢሕአዴግ ሦስት እኅት ድርጅቶችና በአጋርነት የሚታወቁት አምስቱ ድርጅቶች ሊቃነመናብርት የብልጽግና ፓርቲን ውሕደት ስምምነት በፊርማቸው አረጋግጠዋል። ከሕወሓት በስተቀር በኢሕአዴግ ጥላ ሥር የነበሩ ድርጅቶች የብልጽግና ፓርቲ ስምምነት ፊርማቸውን ያኖሩት ዛሬ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ለማ ከመደመር ፍልስፍናንና ከኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች ውሕደት ጋር ተቃርኖ እንዳላቸው ገለጹ

Lemma Megersa and Taye Dendea

አቶ ታዬ ደንደአ፤ አቶ ለማ ምንም ዐይነት ተቃውሞም ኾነ የተለየ ሐሳብ አቅርበው እንደማያውቁ ተናገሩ

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 1, 2019)፦ አሁን ላለው ለውጥ ቀዳሚ ሚና እንዳላቸው የሚታወቁት የመከላከያ ሚኒስትሩና የኦዴፓ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ፣ የመደመር ፍልስፍናንና የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶቹን ውሕደት ያልደገፉት መኾኑን ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦሮሚያ ክልል ለስድስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ሹመት ሠጠ

Chaltu Sanni and Addisu Arega

አዲሱ አረጋ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ ተሹመዋል

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 29, 2019)፦ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ለስድስት ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ሹመት የሠጠ ሲሆን፣ አቶ አዲሱ አረጋና ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ ኾነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሦስት የኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ሹመት ሠጡ

PM Dr. Abiy Ahmed

ሁለቱ ባለሥልጣናት የተሾሙት በሚኒስትር ማዕረግ ነው

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 29, 2019)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለሦስት የመንግሥት ኃላፊዎች ሹመት ሠጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹሙት የሠጡዋቸው አቶ አሕመድ ቱሳ፣ ዶ/ር ዓለሙ ስሜና አቶ አወሉ አብዱ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በነሜ/ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ላይ አዲስና ከባድ የሙስና ክስ ተመሠረተ

Major General Kinfe Dagnew

የተከሰሱት ከ214 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከተገዛና ጥራቱን ካልጠበቀ ራዳር በተያያዘ ነው

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 28, 2019)፦ በነሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ላይ የፌዴራሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አዲስና ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ጠበቃ ይዘው እንዲቀርቡ ቀጥሯቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ደኢሕዴን ብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀለ

Prosperity Party

በብልጽግና ፓርቲ ምሥረታ ላይ ሕወሓት እስካሁን በኦፊሴል ውሳኔዋን አላሳወቀችም

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 28, 2019)፦ ከሕወሓት በስተቀር ሦስቱ የኢሕአዴግ እኅት ድርጅቶችና አምስቱ አጋር ድርጅቶች በሙሉ የብልጽግና ፓርቲን ለመቀላቀል ውሳኔ አሳልፈዋል። ሕወሓት ግን እስካሁን በኦፊሴል ውሳኔዋን አላሳወቀችም፤ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ግን ውሳኔውን የሚወስነው የሕወሓት ጠቅላላ ጉባዔው ነው ተደምጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲሱን ፓርቲ ምሥረታ ሕግን የተከተለ መኾኑን አስታወቁ

PM Dr. Abiy Ahmed (left), Getachew Reda (right)

በፓርቲው ምሥረታ የሚከሱን በአማራጭ ሐሳብ ይሞግቱን ብለዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 28, 2019)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በብልጽግና ፓርቲ ላይ የሚሰሙ ክሶችን ከማቅረብ፤ አማራጭ ሐሳብ ይዞ በመምጣት መሞገት የሚሻል መኾኑንና የአዲሱ ፓርቲ ምሥረታ ሒደት ሕጋዊ ስለመኾኑ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 11ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

EZ weekly news digest, week 11, 2012 E.C

የዓመቱ አሥራ አንደኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከኅዳር 8 - 14 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ሳምንቱ በታሪክም ልናስታውሳቸው የሚችሉ የፖለቲካ ክዋኔዎች የተስተናገደበት ነው። ከእነዚህ ውስጥ ረዥም ዕድሜ ካስቆጠሩት ፓርቲዎችና በሥልጣን ላይ ለ28 ዓመታት የቆየው ኢሕአዴግ በአዲስ ፓርቲ የሚተካ መኾኑን ውሳኔ የተላለፈበት ነው። ብልጽግና የሚለው አዲስ ፓርቲ ሆኖ የዚህች አገር ትልቁ ፓርቲ በመሆን በአዲስ አደረጃጀት እንደሚሠራ ይፋ የተደረገበት ሳምንት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሊባባ በአዲስ አበባ

ጃክ ማ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ዛሬ የአንድነት ፓርክን ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር በመኾን ጎብኝተዋል

አሊባባ ግሩፕ በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ ዓለም አቀፍ የንግድ መገናኛ ማዕከል ለመገንባት የሚያስችለውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመ

ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 25, 2019)፦ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት በዓለማችን ቀዳሚ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የኾነው አሊባባ ኩባንያ ሊቀመንበር ጃክ ማ እና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መጀመሪያ በስዊዘርላንድ፣ ከዚያም በኋላ ሚያዝያ 2011 ዓ.ም. አጋማሽ ላይ በቻይና ተገናኝተው በጋራ ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረው ነበር። በቻይና ሃንግዙ የሚገኝውን የአሊባባ ዋና መሥሪያ ቤት ጠቅላይ ሚንስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በጃክ ማ አስጎብኝነት ተመልክተዋል። ስለኩባንያው አውግተዋል። በውይይታቸው መደምደሚያ ላይ አዲስ አበባ ለመገናኘት ቀን ቆርጠው ይለያያሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ