ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባበል ይደረጋል

Nobel Laureate Abiy Ahmed

ለአዲስ አበባና ለአካባቢዋ ነዋሪዎች ጥሪ ተደርጓል

ኢዛ (ረቡዕ ታኅሣሥ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 11, 2019)፦ በትናንትናው ዕለት የዓለም የሰላም ኖቬል ሽልማትን የተቀበሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ነገ ታኅሣሥ 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ተገለጸ። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ የሚደገው የአቀባበል ዝግጅት ነገ ማለዳ ላይ የሚከናወን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዘጠኝ ፓርቲዎች እውቅና አገኙ

National Electoral Board of Ethiopia (NEBE)

ምርጫ ቦርድ የብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ የሌሎች ፓርቲዎች የእውቅና ጥያቄን እየተመለከተ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ታኅሣሥ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 11, 2019)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእውቅና ሰርቲፊኬት (የምሥክር ወረቀት) መሥጠቱን ቀጥሏል። ዛሬ ለዘጠኝ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መሥጠቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማትና ኢትዮጵያ

Nobel Laureate PM Abiy Ahmed and the First lady

ኢትዮጵያ የገነነችበት ቀን

ኢዛ (ረቡዕ ታኅሣሥ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 11, 2019)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እውቅና የሚሠጠውን የኖቬል ሽልማት (የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማት) በኦስሎ በታላቅ ክብር ተቀብለዋል። ዕለቱ ኢትዮጵያ የገነነችበት ቀን ለመኾን በቅቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 13ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare weekly news digest, week 13, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አሥራ ሦስተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከኅዳር 22 - 28 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ባሳለፍነው ሳምንት ቀዳሚ ፖለቲካዊ ክንውኖች ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ ከብልጽግና ፓርቲ ራሱን ያራቀው ሕወሓት ፌዴራሊስቶች ናቸው ብሎ ያመነባቸውን የፖለቲካ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በማሰባሰብ በመቐለ ለሁለት ቀናት ያካሔደው ጉባዔ አንዱ ነው። በዚህ ጉባዔ ላይ የብልጽግና ፓርቲን የሚቃወሙ የበረከቱ አስተያየቶች የተሰነዘሩበትና የተለያዩ ጽሑፎች የቀረቡበት ሲሆን፣ በዋናነት ግን ከብልጽግና ፓርቲ አኀዳዊ ሥርዓትን ለማስፈን እየሠራ ነው የሚለውን አመለካከት ለማንጸባረቅ የተሞከረበት መድረክ ነው ማለት ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዩኒቨርሲቲዎች በፌዴራል ፖሊስ እንዲጠበቁ ተወሰነ

Addis Ababa University

በተከሰቱ ጥፋቶች እጃቸው ያለበት አካላትን ለሕግ የማቅረብ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል

ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 9, 2019)፦ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በሙሉ በፌዴራል ፖሊስ እንዲጠበቁ መንግሥት ውሳኔ ላይ መድረሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦነግና ኦብነግን የተካተቱበት አስር ፓርቲዎች በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

በጋራ ለመሥራት ተስማሙት አስሩ ፓርቲዎች

አብዛኞቹ በነፃ አውጭነት ትግል ሲያደርጉ የነበሩ ፓርቲዎች ናቸው

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 6, 2019)፦ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) የተካተቱበት 10 የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገር አቀፍ ደረጃ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ዛሬ ተፈራረሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረ የሳይበር ጥቃት ከሸፈ

Ethiopian Information Network Security Agency (INSA)

በአገሪቱ ለሃያ ደቂቃ ኢንተርኔት ተቋርጦ ነበር

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 5, 2019)፦ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረ የሳይበር ጥቃትን ለማክሸፍ ሲባል የአገሪቱ የኢንተርኔት አገልግሎት ለሃያ ደቂቃዎች ተቋርጦ እንደነበር ተመለከተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብልጽግና ፓርቲ የእውቅና ሰርቲፊኬት እንዲሠጠው ለምርጫ ቦርድ አመለከተ

End of EPRDF

ብልጽግና ፓርቲን የመሠረቱት ፓርቲዎች ፍቃድ ይሰረዛል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 4, 2019)፦ በሦስቱ የኢሕአዴግ እኅት ድርጅቶችና በአምስቱ አጋር ድርጅቶች ውሕደት ላይ የተመሠረተው ብልጽግና ፓርቲ የእውቅና ሰርቲፊኬት (የምዝገባ የምስክር ወረቀት) እንዲሠጠው ለምርጫ ቦርድ ጥያቄውን አቀረበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ እንደገና ወደ ዋሽንግተን ሊካሔድ ነው

The Grand Ethiopian Renaissance Dam

የተፋሰሱ አገራት ቀጣይና የመጨረሻ የተባለውን ስምምነት በዚህ ወር መጨረሻ በዋሽንግተን ያካሒዳሉ ተብሎ ይጠበቃል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 4, 2019)፦ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሦስቱ የተፋሰሱ አገሮች እስካሁን ባደረጉት ውይይት ላይ ተመስረተው የመጨረሻ ስምምነት ያደርጉበታል የተባለው የውይይት መድረክ እንደገና በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚካሔድ ለማወቅ ተችሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 12ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare weekly news digest, week 12, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አሥራ ሁለተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከኅዳር 15 - 21 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ሳምንቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ አዳዲስ የሚታዩ የተለያዩ ክስተቶችን አስተናግዶ ያለፈ ነው። ክስተቶቹ አላፊ ናቸው ተብለው የሚታለፉ ሳይሆን፤ በቀጣይ አነጋጋሪ ሆነው የሚቀጥሉ፣ መጨረሻው ምን ይሆን? የሚል ጥያቄ የጫሩ ናቸው ማለት ይቻላል። ከብልጽግና ፓርቲ የምሥረታ ሒደት ጋር ተያይዞ አዳዲስ ክዋኔዎች የተስተዋሉበት ሳምንት መሆኑ አንዱ ነው። ከሕወሓት በስተቀር ሁሉም የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ከብልጽግና ፓርቲ ጋር “ወደፊት!” በሚል ማረጋገጫ የሠጡበትና ይህንንም በየድርጅቶቻቸው በጠቅላላ ጉባዔ በአዲሱ ፓርቲ ምሥረታ ላይ ወስነው ያጠናቀቁበትና በሕብረት የስምምነት ፊርማ ያሳረፉበት ሳምንት ነበር። እንዲህ ካለው ሒደት በተቃራኒ የቆመው ሕወሓት ደግሞ የተቃውሞ ድምፁን በይበልጥ ያሰማበት ሳምንት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ