በጎንደር በጥምቀት በዓል ላይ ከፍተኛ ፍንዳታ ለመፈጸም ያሴሩ ሁለት ግለሰቦች ተያዙ

ጥምቀት በጎንደር

“ለጥቃቱ ያሰማራቸውን አካል በቅርቡ ይፋ አደርጋለሁ” ብሔራዊ የደኅንነት አገልግሎት

ኢዛ (ዓርብ ጥር ፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 17, 2020)፦ የዓለም የማይዳሰስ ቅርስ በመኾን በዩኔስኮ እንዲመዘገብ እውቅና የተሠጠው የጥምቀት በዓል በሚከበርበት ዋዜማ ላይ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርባቸው አንዱ በኾነው በጎንደር በተኩስ የተቀናጀ ከፍተኛ ፍንዳታ ለመፈጸም በዝግጅት ላይ የነበሩ የጥፋት ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሚሸጠው ቴሌ ከእቅዱ በላይ ገቢ እያገኘ ነው

Ethio-Telecom

የስድስት ወር ገቢው ከ22.04 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኗል

ኢዛ (ሐሙስ ጥር ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 16, 2020)፦ በሽያጭ ወደ ግል ይዛወራሉ ተብለው ከሚጠበቁት ግዙፎቹ የመንግሥት ኩባንያዎች ውስጥ አንዱ የኾነው ኢትዮ ቴሌኮም በ2012 በጀት ዓመት በግማሽ ዓመት 22.04 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱንና ይህም በ2011 ዓ.ም. በተመሳሳይ ወቅት ካገኘው ገቢ የ32 በመቶ ብልጫ እንዳለው አመለከተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዩኒቨርሲቲዎች ግጭት ከ35 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ተስተጓጉለዋል

Prof. Hirut Woldemariam

በግጭቶቹ እርምጃ የተወሰደባቸው ከ900 በላይ ናቸው

ኢዛ (ሐሙስ ጥር ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 16, 2020)፦ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚፈጠሩ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች በደኅንነት ሥጋት ከ35 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ትምህርት ገበታቸው ላይ አለመኾናቸው ተመለከተ። ከ900 በላይ ተማሪዎችና የአስተዳደር ሠራተኞች ላይ እርምጃ ስለመወሰዱም ተገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ረቂቅ የምርጫ ሰሌዳውን ይፋ አደረገ

National Election Board of Ethiopia 2020 schedule

ድምፅ መስጫው ቀን ነኀሴ 10 እንዲኾን ቦርዱ አቅዷል

ኢዛ (ረቡዕ ጥር ፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 15, 2020)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ቀጣዩን አገራዊ ምርጫ ለማካሔድ የሚያስችለውን ረቂቅ የምርጫ ሰሌዳውን ይፋ ሲያደርግ፤ የምርጫው ቀን ነኀሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚኾን አመላክቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ኃይለማርያምም ፍርድ ቤት ያልቀረቡ መሆኑ ታውቋል

አቶ በረከት ስምኦን (ከግራ ወደቀኝ)፣ አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የቀድሞው ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝና አቶ ታደሰ ካሣ

የእነ አቶ በረከት የመከላከያ ምስክሮች ቃል መሰማት ጀመረ

አቶ ደመቀ፣ አቶ ገዱና አቶ ኃይለማርያም በመከላከያ ምስክርነት ቢካተቱም አልቀረቡም

ኢዛ (ማክሰኞ ጥር ፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 14, 2020)፦ እነ አቶ በረከት ስምኦን በተመሠረተባቸው ክስ የመከላከያ ምስክሮቻቸውን ዛሬ ማሰማት ጀምረዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 18ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 18, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አሥራ ስምንተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከታኅሣሥ 27 - ጥር 3 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ባሳለፍነው ሳምንት ጐልተው ከሚጠቀሱ ዜናዎች ውስጥ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጦር መሣሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅን ማጽደቁ አንዱ ነው። በዚህ አዋጅ እንደ ሴንጢ፣ ሳንጃ፣ ገጀራ፣ … የመሳሰሉትን አደገኛ በኾነ ሁኔታ መገልገልና በብዛት መያዝ ክልከላ የተደረገበት መኾኑን የሚያመለክት አንቀጽ ያለው ነው። ያለፍቃድ ዘመናዊ ከኾኑ መሣሪያዎች ከጦር ሜዳ መነፅር ጀምሮ የተለያዩ መሣሪያዎችን መያዝ ማከማቸት ማምረትና ማዘዋወር እንደማይቻልም ይደነግጋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ ቦርድ የፓርቲዎችን ምዝገባ የሚደነግገውን መመሪያ አጸደቀ

National Electoral Board Of Ethiopia

መመሪያ ከመጽደቁ በፊት ከፓርቲዎች ጋር የተለያዩ ውይይቶች መደረጋቸው ተገልጿል

ኢዛ (ረቡዕ ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 8, 2020)፦ በወራት ልዩነት በሚካሔደው አገር አቀፉ ምርጫ ዝግጅት እያደረገ ያለው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በአዲሱ የምርጫ ቦርድ አዋጅ መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባን የተመለከተ መመሪያ አወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 17ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 17, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አሥራ ሰባተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከታኅሣሥ 20 - 26 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት ከፖለቲካዊ ጉዳዮች አንፃር ለየት ያለ ክስተቶችን ያስተናገደ ነው ሊባል የሚችል ነው። በጣት የሚቆጠሩ ወራት የቀሩትን አገራዊ ምርጫ የተመለከቱ ቅስቀሳና ይፋዊ የምረጡኝ ዘመቻ ተጀመረ ማለት ነው? የሚል ጥያቄ የሚጭሩ እንቅስቃሴዎች ጐልተው የታዩበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

በአገሪቱ ያለውን ችግር አስወግዶ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ያግዛል ተብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 2, 2020)፦ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየተስተዋለ ያለውን ችግር አስወግዶ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ያግዛል የተባለው የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተሰናዳው ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ