ቦሌ ላይ ኮሮና ቫይረስ ይዟቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ አራት ኢትዮጵያውያን ክትትል እየተደረገላቸው ነው

Coronavirus at Bole international airport

ለተጨማሪ ምርመራ የደም ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኳል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 28, 2020)፦ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከቻይና ዉሃን ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥረው በኳራንቲን ተለይተው ሕክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙና በደም ምርመራ ከአምስት ዐይነት የኮሮና ቫይረስ ነፃ መኾናቸው ቢረጋገጥም፤ የደም ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ መላኩ ዛሬ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 20ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 20, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሃያኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከጥር 11 - 17 ቀን 2012 ዓ.ም.):- ባሳለፍነው ሳምንት አነጋጋሪና ባልተለመደ ሁኔታ መግለጫ ጭምር የወጣበት ጉዳይ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ትእዛዝ የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትርነታቸው መነሳትና በቦታቸው አዲስ ሚኒስትር ከመተካት ጋር ተያይዞ የተከተለው እሰጥ አገባ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጫማ ማምረት ሥራ የሚታወቀው ኦኬ ጃማይካ ጫማ ሥራ አቆመ

OK Jamaica Shoes Factory

ምክንያቱ ለባንክ እዳ አበዳሪው ባንክ ፋብሪካውን በመረከቡ ነው

ኢዛ (ዓርብ ጥር ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 24, 2020)፦ በጫማ ማምረት ሥራ ከሚታወቁ የአገር ውስጥ ፋብሪካዎች በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት ተርታ አንዱ የኾነውና ኦኬ ጃማይካ ጫማ ፋብሪካ ሥራ እንዳቋረጠ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቻይና አደገኛ ገዳይ በሽታ ገጠማት

ዉሃን ከተባለች የቻይና ግዛት የተነሳው ኮሮና ቫይረስ

ኢትዮጵያም ያሰጋታል ተባለ

ኢዛ (ዓርብ ጥር ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 24, 2020)፦ ዓለማችን ተዛማችና በፍጥነት የሚተላለፍ የሰው ልጆች ገዳይ የኾነ በሽታ በተደጋጋሚ ገጥሟታል። ከነዚህ በሽታዎች ውስጥ ኤድስ፣ ኢቦላና ሳርስ የሚጠቀሱ ሲሆኑ፤ ከነዚህ ውስጥ ኤድስ የአጥቂነቱ ዕድሜ እየተራዘመ ሲሔድ ሌሎቹ ግን በቁጥር ስር ሊውሉ ወይም ሊጠፉ ችለዋል። በቅርቡ ደግሞ መነሻው ቻይና የኾነው ኮሮና ቫይረስ ዓለምን በሥጋት ወጥሯት ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእስክንድር ነጋ ይመራል የተባለው ፓርቲ ጊዜያዊ እውቅና ተሠጠው

ባልደራስ

ሦስት ፓርቲዎችም በተመሳሳይ ተመዝግበዋል

ኢዛ (ረቡዕ ጥር ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 22, 2020)፦ በጋዜጠኛና አክቲቪስት እስክንድር ነጋ የሚመራው “ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ” ፓርቲና ሦስት ሌሎች ፓርቲዎች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ (ሰርቲፊኬት) እና ጊዜያዊ እውቅና እንደተሠጣቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕወሓት ም/ሊቀመንበርና የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሯ ከኃላፊነትቸው ተነሱ

ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ)

ሦስት አዳዲስ ሚኒስትሮች ተሹመዋል

ኢዛ (ረቡዕ ጥር ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 22, 2020)፦ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር በመኾን ከጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያገለግሉ በቆዩትና የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር የኾኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ምትክ አዲስ ሚኒስትር ተሾሙ። ለሁለት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችም አዳዲስ ሚኒስትሮች ተሹመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 19ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 19, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አሥራ ዘጠነኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከጥር 4 - 10 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት ዐቢይ ዜና በመኾን በቀዳሚነት ሊጠቀስ የሚችለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለስድስተኛው አገራዊ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ማድረጉ ነው። ቦርዱ ያሰናዳውን የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ተከትሎ ከባለድርሻ አካላት ጋር የመከረበትም ወዲያው ነው። ይሁንና የጊዜ ሰሌዳው በተለያዩ ወገኖች የተለያዩ አስተያየቶች እየተሠጠበት ይገኛል። እነዚህ አስተያየቶች በርካታ ጉዳዮችን እያመላከቱ ነው። ቀጣዩን የምርጫ ሒደት በምን መልኩ ይካሔድ የሚለውን አመለካከት የተለያየ እንዲሆን አድርጓል። ምርጫ ቦርድ ግን የተጣበበውን ጊዜ በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ በማመን፤ የጊዜ ሰሌዳውን በማውጣት እንዲመከርበት ማድረጉ በትክክል ምርጫው ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ የሚካሔድ መኾኑን ያሳየበት ስለመኾኑም ተገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጎንደር ለጥምቀት በዓል ለታዳሚዎች የተሰናዳ ርብራብ በመደርመሱ ጉዳይ ደረሰ

Gonder Timket 2020

አሥር ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ ከመቶ አርባ ሰዎች በላይ ተጎድተዋል

ኢዛ (እሁድ ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 20, 2020)፦ የጥምቀት በዓል በድምቀት ሲከበርባት የዋለው ጎንደር፤ በዓሉ በሚከበርበት ሥፍራ በጥንታዊው የአፄ ፋሲል ገንዳ አካባቢ ለበዓሉ ታዳሚዎች በአጣና ርብራብ የተሰናዳ ማረፊያ (ማማ) ተደርምሶ አሥር ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ፤ ከአንድ መቶ አርባ ሰዎች በላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለስድሳ አምስት መኮንኖች የተለያዩ የጄኔራልነት ማዕረጎች ተሠጡ

ፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለጄኔራሎቹ ማዕረግ ሲሠጡ

ሹመቱን የሠጡት ፕ/ት ሣህለወርቅ ዘውዴ ናቸው

ኢዛ (እሁድ ጥር ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 19, 2020)፦ በጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አቅራቢነት ለ65 መኮንኖች የተለያዩ የጄኔራልነት የማዕረግ ሹመቶች ተሠጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በህዳሴ ግድብ ላይ በዋሽንግተን የተደረገው ውይይት መቋጫ እያነጋገረ ነው

thiopia's Grand Renaissance Dam

ከሁለት ሳምንት በኋላ የመጨረሻ ስምምነት ይጠበቃል

ኢዛ (ሐሙስ ጥር ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 16, 2020)፦ ባለፉት ሁለትና ሦስት ወራት በተከታታይ በተደረጉ ውይይቶች ላይ ስምምነት ሳይደርሱ የቀሩት ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በህዳሴ ግድብ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ በዋሽንግተን ያካሔዱትን ውይይት ቢያጠናቅቁም የደረሱበት ድምዳሜ ግን ብዥታ ፈጥሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ