ቴዲ አፍሮ የፍቅር አሸናፊነት የታየበት መድረክ

Teddy Afro Concert 2020

መቶ ሃምሳ ሺሕ ታዳሚዎች የተገኙበት

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 24, 2020)፦ ባሳለፍነው ሳምንት ማለቂያ ላይ ቅዳሜ የካቲት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. አዲስ አበባ ደምቃ ያመሸችበት ነበር። በመቶ ሃምሳ ሺሕ የሚቆጠሩ ታዳሚዎችን በአንድ ቦታ በማሰባሰብ የደመቀ የሙዚቃ ድግስ ያጣጣሙበትን ምሽት አሳልፈዋል። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ የገነነ ስም ያለው ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) በመስቀል አደባባይ በተሰናዳው በልዩ ሁኔታ በታነፀው መድረክ ላይ፤ በቦታው የነበሩ የሙዚቃ አድናቂዎቹን አጀብ ባሰኘ የመድረክ አያያዝ ጭምር አስደስቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአምቦ ጥቃት የኦነግ ሸኔ እጅ እንዳለበት የፖሊስ ገለጸ

ኮሚሽነር አራርሳ መርደሳ

በቡራዩ ግድያም የኦነግ ሸኔ አባሎች መኾናቸው ተጠቁሟል

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 23, 2020)፦ በአምቦ የተፈጸመውን የቦምብ ጥቃት በኦነግ ሸኔ የተፈጸመ ስለመኾኑ ተጠቆመ። ይህንን የገለጹት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር ጥቃቱን ካደረሱት ተጥርጣሪዎች መካከል ይህንን የሚያረጋግጥ መረጃ በመገኘቱ ነው ብለዋል። በቡራዩ ግድያም የኦነግ ሸኔ አባሎች መኾናቸው ተጠቁሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአምቦ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦምብ መወርወሩ ተሰማ

በአምቦ ለብልጽግናና ለዶክተር ዐቢይ የተካሔደው የድጋፍ ሰልፍ በከፊል

ከ20 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 23, 2020)፦ ዛሬ ጠዋት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድና ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ በአምቦ በተካሔደው ትዕይንተ ሕዝብ መሐል ቦምብ ተውርውሮ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቡራዩ ጥቃት ተጠርጣሪዎች እየተያዙ ነው

Solomon Tadese

እስካሁን 17 ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 22, 2020)፦ ባለፈው ዓርብ የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በቡራዩ ከተማ የደረሰውን ጥቃት በማቀነባበርና በመተግበር ተሳታፊ በመኾን የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ስለመዋላቸው እየተገለጸ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፖለቲካ የጋራ ጥምረት ምርጫው መደረግ የለበትም አለ

Ethiopian Political Parties Joint Council

በዕለቱ 52ቱ ፓርቲዎች ተገኝተዋል

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 21, 2020)፦ 74 የፖለቲካ ድርጅቶች የያዘው “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት” ቀጣዩ አገራዊ ምርጫ 2012 መካሔድ የለበትም የሚል ውሳኔ ላይ መድረሱን አስታወቀ። ድምፅ የሠጡበት ዕለት 52ቱ ፓርቲዎች ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቡራዩ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በታጣቂዎች ተገደሉ

Solomon Tadese

አብረዋቸው የነበሩ ቆስለዋል

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 21, 2020)፦ ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ የቡራዩ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በታጠቁ ኃይሎች ተተኮሰባቸው ሲገደሉ፤ አብረዋቸው የነበሩ የፖሊስ አዛዥም በጥይት መመታታቸው ተገለጸ። ይህ አሳዛኝ ድርጊት የተፈጸመው የቡራዩ ከተማ የጸጥታ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰና ሌሎች ሰዎች ምሳ በመብላት ላይ እያሉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ ሥራ አስፈፃሚ ተሾመ

አቶ አሸብር ባልቻ

ዶክተር አብርሃም በላይ ተሸኙ

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 21, 2020)፦ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሹመት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በመኾን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚነታቸው በለቀቁት በዶክተር አብርሃም በላይ ምትክ አዲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተሾመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮና “ኢትዮጵያ ወደ ፍቅር”

“ኢትዮጵያ ወደ ፍቅር” የተሰኘው የቴዲ አፍሮ ኮንሰርት

ከመቶ ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይጠበቃሉ

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 21, 2020)፦ ኢትዮጵያ ወደፍቅር የሚል መጠሪያ የተሠጠው የታዋቂው አቀንቃኝ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኮንሰርት ነገ የካቲት 14 ቀን 2012 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ይደረጋል። ኮንሰረቱን ከመቶ ሺህ ሰዎች በላይ ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ400 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለውና ተሰርቆ የነበረ የኢትዮጵያ ዘውድ ወደ አገሩ ተመለሰ

አቶ ሲራክ አስፋው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዘውዱን ሲያስረክቡ፣ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም.

ኢሕአዴግ ሥልጣን በያዘ በሁለተኛ ዓመቱ ነበር የተሰረቀው

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 20, 2020)፦ ኢሕአዴግ ሥልጣን በያዘ በሁለተኛ ዓመቱ በ1985 ዓ.ም. ተሰርቆ የነበረውና ከ400 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው የኢትዮጵያ ዘውድ በዛሬው ዕለተ ለኢትዮጵያ ተመለሰ። ዘውዱ የተዘረፈው መቀሌ አካባቢ ከሚገኘው የሥላሴ ጨለቆት ቤተ ክርስቲያን እንደኾነ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰማእታት ቀን ዛሬ 83ኛ ዓመቱ ተከበረ

የሰማእታት ቀን

አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የፋሺስት ጣሊያን የጦር መሪ ጄኔራል ላይ ቦንቦች የወረወሩባት ዕለት ነች

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 20, 2020)፦ በ1929 ዓ.ም. ልክ በዛሬዋ ዕለት (የካቲት 12 ቀን)፤ የፋሺስት ጣሊያን የጦር መሪ ጄኔራል ሩዶልፍ ግራዚያኒ በቤተመንግሥት የአዲስ አበባን ሕዝብ ጠርቶ ንግግር ሲያደርግ፤ ኢትዮጵያ በመወረሯ ሲቃጠሉ የነበሩ ሁለት ጀግና ወጣቶች የእጅ ቦንብ በመወርወር የመግደል ሙከራ ያደረጉባት ቀን ናት። የአገራቸው ጉዳይ ያንገበገባቸው ወጣቶቹ፤ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ናቸው። ይኽ ከኾነ ዛሬ 83ኛ ዓመቱ ነው። ዕለቱም “የሰማእታት ቀን” እየተባለ ይከበራ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ