ኢዜማ ከ18 ሺህ በላይ የአባላት ፊርማ በማሰባሰብ ለምርጫ ቦርድ አስገባ

Ethiopian Citizens for Social Justice

እንደአዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ምስክር ወረቀት ለማግኘት እየተጠባበቀ ነው

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 1, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ድርጅቶች እንዲያሟሉ ከጠየቃቸው ዝርዝር ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የኾነውን አንድ አገር አቀፍ ፓርት 10 ሺህ የአባላት ፊርማ ለምርጫ ቦርድ ማስገባት ሲሆን፤ ኢዜማ ከ18 ሺህ በላይ የአባላት ፊርማ ያለበትን ሰነድ ማቅረቡን አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ተቋቋመ

ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ አቶ አሕመድ ሽዴና አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

አባላቱ ስድስት ሲሆኑ፣ ሁሉም በሚኒስትር ማዕረግ ያሉ ባለሥልጣናት ናቸው

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 29, 2020)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሔደው 80ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ክትትል የሚያደርግ ስድስት አባላት ያሉት ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ማቋቋሙን የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሜሪካ በግድቡ ውኃ ሙላት ላይ የሠጠችው መግለጫ አስቆጥቷል

The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)

የኢትዮጵያ መንግሥት በጉዳዩ ላይ መግለጫ ሠጠ

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 29, 2020)፦ የአሜሪካ መንግሥት በህዳሴ ግድብ ዙሪያ እየተደረገ ያለው ድርድር መቋጫ ባላገኘበትና ምንም ዐይነት ስምምነት ሳይካሔድ በህዳሴ ግድብ ውኃ መሙላት መጀመር የለበትም፤ ሙከራም መደረግ የለበትም የሚል ሐሳብ ያለው መልእክት ማስተላለፉን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግሥት ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመላው አገሪቱ የተፈጠረው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ መንሥኤው አልታወቀም

Addis Ababas tram

በጉዞ ላይ የነበሩ ባቡሮች ባሉበት ለመቆም ተገድደዋል

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 28, 2020)፦ ዛሬ በኢትዮጵያ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች እስካሁን ምክንያቱ በትክክል ባልታወቀና ባልተለየ ሁኔታ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቱ ተቋርጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች ቁጥር 11 መድረሱን ስዊድን አስታወቀች

Coronavirus in Sweden

በዛሬው ዕለት አራት፣ ትናንት ደግሞ አምስት ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል ተባለ

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 28, 2020)፦ በዛሬው ዕለት አራት ሰዎች በሦስት የተለያዩ ከተሞች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የስዊድን መገናኛ ብዙኀን ዘገቡ። በትናንትናው ዕለት ደግሞ አምስት ሰዎች፣ ከትናንት በስቲያ አንድ፣ ከሳምንታት በፊት አንድ ሰው በቫይረሱ የተያዙ መኖራቸው ታውቋል። እስካሁን በስዊድን በቫይረሱ የተያዙት ቁጥር አስራ አንድ ደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዴፓ ቢሮዎቹ እንዲመለሱለት ምርጫ ቦርድ ትእዛዝ አስተላለፈ

የኢዴፓ አመራሮች ጋዜጣዊ

ቢሮዎቹ የሚመለሱት አቶ ልደቱ ያሉበት ኢዴፓ ነው

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢዴፓ (የኢትዮጵያዊያን ዴሞክራቲክ ፓርቲ) አመራር ቢሮዎቹ እንዲመለሱለት ማሳሰቢያ ሠጠ። ቢሮዎቹ እንዲመለሱለት ምርጫ ቦርድ የወሰነለት፤ አቶ ልደቱ አያሌው ያሉበት ኢዴፓ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብና በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ የአሜሪካ መንግሥትን አድሎአዊ ጣልቃ ገብነት በዋሽንግተን ተቃወሙ

“ድሃ ወገኖቻችን አንጀታቸውን ቋጥረው በሠሩት ግድብ አንደራደርም!”

“ዓባይ የእኛም ጭምር ነው” ኢትዮጵያውያን

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ የአሜሪካ መንግሥት አድሎአዊ ጣልቃ ገብነት በመቃወም፤ ኢትዮጵያውያን በዋሽንግተን ዲሲ የሚካሔደው ሰልፍ ተጀምሯል። በዚህ ሰልፍ ላይ ኢትዮጵያውያን “ዓባይ የእኛም ጭምር ነው!” ሲሉ ተደምጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ልማት ባንክ የተበላሸ ብድሩን ከ40 ወደ 34 በመቶ ማውረዱን ገለጸ

Development Bank of Ethiopia

በአራት ዓመት ውስጥ የተበላሸ ብድሩን 10 በመቶ ለማድረስ አቅዷል

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተበላሸ የብድር መጠኑን ከ40 በመቶ ወደ 34 በመቶ ያወረደ መኾኑን ዛሬ የባንኩ ባለሥልጣን በሠጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብሮድባንድ ኢንተርኔት ዋጋ እስከ 72 በመቶ ቀነሰ

Ethio Telecom

ኢትዮ ቴሌኮም በመኖሪያ ቤታቸው ለሚጠቀሙት ደንበኞቹ 69 በመቶ ቅናሽ አደረገ

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው የቴሌኮም ድርጅት በመኾኑ የሚታወቀው ኢትዮ ቴሌኮም፤ በብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎቱ ላይ የዋጋ ቅናሽ እንዳደረገ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ዮሐንስ ቧያለው አዲሱ ሹመት እንደማይቀበሉ አሳወቁ

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ከአማራ ማስ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ

የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ኾነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሾሙት ትናንት ነበር

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 26, 2020)፦ በትናንትናው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት እንዲኾኑ የተሾሙት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፤ ሹመቱን ለመቀበል እንደሚቸገሩ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ