የ2012 ዓ.ም. 26ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች
የዓመቱ ሃያ ስድስተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች
ኢዛ (ከየካቲት 23 - 29 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ባሳለፍነው ሳምንት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያና ግብጽ የገቡበት የቃላት ጦርነትን የሚስተካከል የለም። ሳምንቱን ሙሉ በዚህ ጉዳይ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ቀዳሚውን ሥፍራ የያዙ ናቸው። የአገር ውስጥ ሚዲያዎች የመክፈቻ ዜናዎቻቸው በዚሁ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ያነጣጠረ ነው። የህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለና ግንባታው ተጀምሮ አሁን ያለበት ደረጃ እስኪደርስ ድረስ ውስጥ ውስጡን ካልኾነ በቀር በግብጽና በኢትዮጵያ መካከል ጠንከር ያለ የቃላት ምልልስ የተደረገበት ጊዜ አልነበረም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...



