ህወሃት/ኢህአዴግ በሲድኒ የጠራው ስብሰባ በተቃውሞ ተወጥሯል

አርቲስት አይናለም ተስፋዬን ጨምሮ 12 ሰዎች ብቻ ወደ አዳራሹ ገብተዋል
Ethiopia Zare (አርብ የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም Feb. 17, 2014)፦ በአውስትራሊያዋ ሲድኒ በአምባሳደር አረጋ ሃይሉ የተጠራው ልማታዊ ውይይት በሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን ተቃውሞ በማሰማት ላይ መሆንቸውንና የመንግስት ደጋፊዎች በቦታው ለመታየት እንዳልቻሉ ለማወቅ ተቻለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ31 ዓመቱ ወጣት ረዳት አብራሪ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ጠለፈ

ጠላፊው ለአምስት ዓመታት በአየር መንገዱ አገልግሏል”መንግሥት

”በጠለፋው ሳይሆን ተሳፋሪዎቹን በማገቱ እስከ 20 ዓመት ሊያሳስር የሚችል ክስ ሊመሰረትበት ይችላል”የስዊስ አቃቤ ሕግPolice search passengers after helping them disembark from the hijacked Ethiopian Airlines flight

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 17, 2014)፦ ዛሬ ጠዋት ሮም ሊገባ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ”ኢቲ 702” በ31 ዓመቱ ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ተገኝ ተጠልፎ በስዊዘርላንድ፤ ጄኔቭ ከተማ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ አረፈ። በጣሊያንና ስዊዘርላንድ ድንበር አካባቢ ሲደርስ በሁለት ተዋጊ ጀቶች ታጅቦ የነበረ ሲሆን፣ ረዳት አብራሪው በስዊዘርላንድ ጥገኝነት ጠይቋል። ተሳፋሪዎቹ አውሮፕላኑ መጠለፉን አያውቁም ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አለማየሁ አቶምሳ በገዛ ፍቃዳቸው ከሥልጣናቸው ለቀቁ

Alemayehu Atomssa, አቶ አለማየሁ አቶምሳEthiopia Zare (ሰኞ የካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 17, 2014)፦ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኦሕዴድ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ። በዛሬው ዕለት በተካሄደው የኦሮሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ መልቀቂያቸውን ያስገቡት አቶ አለማየሁ አቶምሳ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቶ ከሥልጣን መነሳታቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሸንጎ 'በአማራው' ላይ ያነጣጠረውን የዘር ጥላቻ አወገዘ

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) Ethiopian People's Congress for United Struggle (Shengo)Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 5 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 12, 2014)፦ የአማራ ክልል ም/ፕሬዝዳንት አቶ አለምነው መኮንን በአማራው ላይ የሰነዘሩትን ፀያፍና በዘር ጥላቻ ላይ ያዘነበለ ስድብ በማውገዝ፤ "የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ" ትናንት የካቲት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. መግለጫ አወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቫንኩቨር በሳኡዲ አረቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኞች 10 ሺህ ዶላር ተሰበሰበ

Ethiopia Zare (እሁድ ጥቅምት 11  ቀን 2006 ዓ.ም. Jan 18, 2014)፦ በሳኡዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያኖች ያሉበት አሳሳቢ ሁኔታ ያስጨነቃቸው በቫንኩቨር ካናዳ ነዋሪዎች ምሽቱን ባደረጉት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ወደ 10ሺህ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ማሰባሰባቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርኤል ሻሮን ዛሬ አረፉ

እስራኤልን ለአምስት ዓመታት መርተዋል
አርኤል ሻሮን  Ariel SharonEthiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 3 ቀን 2006 ዓ.ም. Jan 11, 2014)፦ የእስራኤል የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር የነበሩትና ሀገሪቷን ለአምስት ዓመታት ያህል የመሩት አርኤል ሻሮን በሰማንያ አምስት ዓመታቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፈረሰኛ ሻምበል ማሩ መልካ በ87 ዓመታቸው አረፉ!

ፈረሰኛ ሻምበል ማሩ መልካ Maru Melkaየቀብር ስነ ስርአታቸው ዛሬ በየካ ሚካኤል ይፈጸማል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ታህሣስ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. Jan 8, 2014)፦ በፈረስ ግልቢያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በአስተማሪነት፣ በስፖርተኝነትና በርካታ ሽልማቶችን በመቀዳጀት ግምባር ቀደም ተጠቃሽ የሆኑት ፈረሰኛ ሻምበል ማሩ መልካ በ87 ዓመታቸው ታህሣስ 29 ቀን 2006 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን ዛሬ የቀብር ስነ ስርአታቸው በአዲስ አበባ የካ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈጸም ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

17ኛው ዓመት የኢትዮጵያዊያን ስፖርት ውድድር በድምቀት ተከናወነ!

በአውስትራሉያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን መካከል በየዓመቱ የሚደረገው የስፖርት ውድድር ዘንድሮም ለ17ኛ ግዜ ከዲሴምበር 24 እስከ 29 ባለት 6 ቀናት በድምቀት ተከናውኗል። በዘንድሮው ውድድር ከመቼውም ግዜ በበለጠ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኢትዮጵያዊ የተሳተፈበት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታላቁ የነፃነት አባት ኔልሰን ማንዴላ አረፉ (1918-2013)

የዓለማችን ታላቁ የፀረ-አፓርታይድ መሪ
ኒልሰን ማንዴላ Nelson Mandela

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሕዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም. Dec 5, 2013)፦ አፓርታይድን ከምድረ ደቡብ አፍሪካ እስከመጨረሻው ለመገርሰስ በተደረገው ታላቅ ተጋድሎ በዋንኛነት ተጠቃሽ የነበሩትና የሰላም አባት በመባል ዓለም አቀፋዊ ሽልማቶችን የተጎናጸፉት የደቡባዊት አፍሪካ የነፃነት አባት ኔልሰን ማንዴላ አረፉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የሳዑዲ መንግሥት በሕግ ሊጠየቅ ይገባል" በፍሎሪዳ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን

እሁድ ኖቨምበር 24 ቀን 2013 (እ.ኤ.አ.) በፍሎሪዳ ስቴትስ በምትገኘው ታምፓ ቤይ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት በሳዑዲ ዐረቢያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ኢሰብዓዊ በደል ከልብ እንዳስቆጣቸው ገልጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ