አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተላልፈው ተሰጡ

“የተፈጠረው ሁናቴ እጅግ ቢያሳዝንም ይህንን አለማቀፍ ህግ የሚጥስ አገዛዝ ለመጣል ሁላችንም ቆርጠን እንድንነሳ ያደርጋል” አቶ ነአምን ዘለቀ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሰኔ 26 ቀን 2006 ዓ.ም. July 3, 2014)፦ ከዱባይ ወደ አስመራ በመጓዝ ላይ የነበሩትና የመን ውስጥ ሰንዓ ከተማ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለትራንዚት የወረዱት የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እዛው የመን ታግተው ከቆዩ በኋላ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው መሰጠታቸው ተረጋገጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን እገታ መፍትሄ አላገኘም

ወደ ኢትዮጵያ እንዳይተላለፉ ስጋቱ አይሏል

“ኤርትራዊያኖች የየመን አየር መንገድን እንዳይጠቀሙ ማስተባበር ያስፈልጋል” አቶ ዳንኤል ጥላሁን (የህግ ባለሙያ)

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሰኔ 26 ቀን 2006 ዓ.ም. July 3, 2014)፦ የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለጉዞ መሸጋገሪያ የመን ከገቡ ጀምሮ በአገሪቱ ደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸውን አስመልክቶ ኢትዮጵያዊያን ቁጣቸውን እያሰሙ ሲሆን በተለይ የየመን አየር መንገድን በመቃወም ኤርትራዊያን የጉዞ ማእቀብ እንዲያደርጉ አንድ ተቀማጭነቱን ካናዳ ያደረገ የህግ ባለሙያ ጥሪ አቀረበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫንኩቨር የኢ/ኦ/ተ ምእመናን እንባችን ታበሰ አሉ

"የጳጳሳት ስራ ሕዝብን ማጽናናት እንጂ ህዝብን ማሳዘን አይደለም" አቡነ መቃርዮስ (ሊቀጳጳስ)
"እረኛው በጎቹን መፈለግ ትቶ በጎቹ እረኛውን የሚፈልጉበት ግዜ መጣ" አቶ አስራት ተሾመ (የሰበካ ጉባኤው ሊቀመንበር)
የቫንኩቨርና አካባቢው ምእመናን

ለላፉት ሶስት አመታት በተለያዩ አለመግብባቶች ሲጓተት የነበረው የቫንኩቨር ጼዴንአ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በአቡነ መቃርዮስ፤ ሊቀጳጳስ ባራኪነት ተከበረ፤ የቫንኩቨር ምእመናን የደስታ እንባ አነቡ። ባለፈው ቅዳሜ እና እሁድ በተከበረው በዓል ላይ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቫንኩቨርና አካባቢው ምእመናን፤ ከአመታት ልፋትና ጸሎት በኋላ ሀሳባቸው ሰምሮ የመድሄኔዓለምና የቅድስት ማርያም ጽላት ስለገቡላቸው ደስታቸውን በዝማሬና በእንባ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእምነት ክህደት ቃል በኃይል አስፈርመዋቸዋል

መዝገቦቹ መልሰው ተቀራረቡ

ጽዮን ግርማ

የሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን የሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. የፍርድ ቤት ቀጠሮ

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በስድስቱ ጦማሪያንና በሦስቱን ጋዜጠኞች ላይ የፌደራል ፖሊስ የተለያየ ምክንያት እየሰጠ ቀጠሮ የሚያራዝመውን ሁለት መዝገብ አንዴ ሲያቀራርበው መልሶ ደግሞ ሲያራርቀው ቆይቶ አሁን ደግሞ መዝገቦቹን መልሶ አቀራርቧቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ ለሃዋርያዊ አገልግሎት ወደ ቫንኩቨር አቀኑ

ብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ Abune MekariosEthiopia Zare (አርብ ሰኔ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. June 27, 2014)፦ በቫንኩቨር ካናዳ የምትገኘውን የጼዴነያ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት የሚከብርበትንና ታቦተ ህጉን ከመንበሩ ለማስገባት ወደ አካባቢው ሀዋርያዊ ጉዞ የሚያደርጉት ብጹእ አቡነ መቃርዮስ ነገ በስፍራው የወንጌል ትምህርት እንደሚሰጡ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወጣቶቹና - ቅዳሜ

አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት
በዛሬው ችሎት ፖሊስ የሃያ ስምንት ቀን የምርምራ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደለት

ጽዮን ግርማ

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፉ ብርሃነ Journalist Tesfalem Weldeyes, Zelalem Kibret, journalist Asmamaw H/ghiorgis, journalist Edom Kassaye, Natnael Feleke and Atnaf Berhane

ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ”ቅዳሜ” ትርጉም አላት። የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ”ቅዳሜ”ን ደግሞ እንደየምድቡ ይውልባታል። እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት። ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሦስተኛዋን ”እሁድ” - በአራዳ ምድብ ችሎት

ጽዮን ግርማ
ሦስተኛዋን ”እሁድ” - በአራዳ ምድብ ችሎት

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ስድስቱን ጦማሪያንና ሦስቱን ጋዜጠኞች በሰንበት ቀን ለሚሰየም ተረኛ ችሎት መቅጠሩን የተለመደ አድርጎታል። ከቀናት በፊት በሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ላይ በተሰጠው የዐሥራ አራት ቀናት የጊዜ ቀጠሮ መሠረት የቀጠሮው ቀን ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ነበር። ዛሬ በዚህ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የነበረውን ሁኔታ መከታተል ባልችልም ምንጮቼ የነገሩኝን ዝርዝር እንዲህ ጽፌዋለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እሁድን በአራዳ ምድብ ችሎት

Journalist Tsion Girma, ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ
ጽዮን ግርማ
This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ለዛሬ የተቀጠሩትን ሦስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን መዝገብ ለማየት የተሰየመው የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች ችሎት ሳይገቡ ነበር። ከመጀመሪያው ችሎት በኋላ ችሎቱ ባለው ቦታ ልክ ቤተሰብ እንዲገባ ተፈቅዶ የነበረ ቢኾንም ዳኛዋ የዕለቱን ሥራ ሲጀምሩ ስለዚህ ጉዳይ የሚያውት ነገር ያለ አይመስልም። ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪ የሚሰየሙት ዳኞች ተረኛ ዳኞች በመኾናቸው የዛሬዋ ዳኛም ለመዝገቡና ለጉዳዩ አዲስ ነበሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቅዳሜን በአራዳ ምድብ ችሎት

Journalist Tsion Girma, ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ
ጽዮን ግርማ
This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ቀኑ ቅዳሜ በመኾኑ ፒያሳ በሚገኘው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግቢ ውስጥ ከዘጠኙ ተጠርጣሪ ቤተሰቦች ውጪ መደበኛ ችሎት ሊከታተል የመጣ ሌላ ሰው አልነበረም። ከሁለት ሰአት ተኩል ጀምሮ ሲጠራቀም የቆየው የችሎት ተከታታይ ቀስ በቀስ በርከት ብሎ በግቢው መታየት ጀመረ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሁለት ቀናት ክራሞት በአራዳ ምድብ ችሎት

ጽዮን ግርማ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.(በፋክት መጽሔት የታተመ)
የታሰሩት ስድስቱ ጦማሪያንና (Bloggers) ሦስቱ ጋዜጠኞች 3 jailed journalists and 6 bloggers
ሚያዚያ 17 እና ሚያዚያ 18 ቀን 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር የዋሉት ስድስቱ ጦማሪያንና (Bloggers) ሦስቱ ጋዜጠኞች በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) ከታሠሩ ዛሬ ሃያ ሦስተኛ ቀናቸውን ይዘዋል። በእነዚህ ጊዜያት ውስጥም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት በጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ሁለት ጊዜ ቀርበዋል። እሁድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀርቡ ብቻቸውን በመኾኑም የፍርድ ቤቱ ድባብ ምን ይመስል እንደነበር የሚያውቅ አንድም ታዛቢ ሰው አልነበረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ