“ፋኖ” ብለን “ሞረሽ” ብለን (በላይ መታፈሪያ)

“ፋኖ” ብለን “ሞረሽ” ብለን

በላይ መታፈሪያ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  

የዘር ፖሊሲ ጎጠኛ አምባገነናዊነት፣

የወያኔ ግፍ ጭቆና አረመኔ ሥርዓት፣

በወገን ላይ ትልቅ ውድቀት፣

ታሪክ አሳናሽ ከፋፋይነት፣

ጥላቻና መለያየት አጎልብቶ በቅጥፈት። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዳግማዊ ዳዊት እና የደሳለኝ በርሄ ሙግት በግጥም (ክፍል ፩)

ዳግማዊ ዳዊት “ፍቺውና ላግባሽ” በሚል ርዕስ ለገጠመው ግጥም፤ ደሳለኝ በርሄ “ዳግማዊ ዓይኑ ይጥፋ!” በሚል ርዕስ በግጥም ምላሽ ሰጥቶታል። በግጥም መመላለስ ብዙ የተለመደ ባይሆንም፤ ገጣሚዎቻችን የሃሳብ ጦርነታቸውንም ሆነ መደጋገፋቸውን ቢያዘወትሩ መልካም ነው ብለን እናምናለን። ሁለቱንም ግጥሞች አቅርበናቸዋል። መልካም ንባብ!!!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀለበቴን ስጧት (በልጅግ ዓሊ)

በልጅግ ዓሊ

“አቤት! አቤት! ደስ ማለቱ፣

አቤት! አቤት! ደስ ማለቱ፣

ያ ምንደኛ የኢህአፓ ቅጥረኛ፣

በቀይ ሽብር ተመትቶ መንገድ ላይ ሲተኛ”

- የፋሺስቶች መዝሙር 1970 ዓ.ም.

የከርቸሌ ፍርደኛ ከወትሮው ለየት ያለ ኀዘን ሰፍሮበታል። የወቅቱ አስከፊ ገጽታን የማይገነዘቡ የወንጀል እስረኞች እንኳን አዘውትረው ከሚያወሩት የሌብነት ገድል ተቆጥበዋል። ምን ትሆን ይሆን? የሚለው ጥያቄ በእያንዳንዱ እስረኛ አዕምሮ ውስጥ ይጉላላል። የልጅቷን የደስ ደስ የማያውቅ የለም። ለባሏ ያላት ፍቅር ደግሞ የተደነቀና እያንዳንዱ እስረኛ የራሱ የሚመኛት ዓይነት ሚስት ናት። እሁድ እሁድ ሕፃን ልጃቸውን ታቅፋ ለጥየቃ ሰልፍ ለመያዝ በሌሊት ነው የምትደርሰው። እሁድ ብዙ ምግብ ስለሚመጣ የምግቡን ማጣት የምታስተጓጉለው ሰኞ ሰኞ ነው። እሱም በግድ በእስረኛው ልመና።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሌቱ እስኪነጋ (አንዱዓለም በቀለ)

ሌቱ እስኪነጋ

አንዱዓለም በቀለ - ከስዊዘርላንድ

ጆሮ አልሰማ አይል - ብዙ ጉድ ይሰማል፥

ቴዲ ታስሯል ብለው - ሲገርመኝ ሰንብቷል፥

ደግሞ አሁን ተፈታ - ብለው ይነግሩኛል፥

በቃ አሁን ይብቃ - ተዉ ዝም በሉ፥

“የሌባ ዓይነ ደረቅ” - ሆኖ እንጂ ነገሩ፥

ለኔ እንደሚገባኝ - ወዲ ነው ሚስጥሩ፥

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሠላም (ቦጋለ ዳኜ)

ሠላም 

ቦጋለ ዳኜ - ከካሊፎርንያ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  

“ዘብ! ተጠ ... ንቀቅ!

ብረ ... ት አውጣ!

ለግርማዊ ጃንሆይ

በብረት ሠላ ... ም በል!

ብረ ... ት አውርድ!

አሳ ... ርፍ!”

ሙሉውን አስነብበኝ ...