ፕሬዝዳንቷ ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል አሉ

Ethiopian President Sahle-Work Zewde

ዘርና ሃይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሐን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ፤ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 31, 2019)፦ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ለአገርና ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረውና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር መጣሱን በመግለጽ፤ ይህ ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ መንግሥት ይሠራል” የጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት

Mr. Nigussu Tilahun, Press Secretary of the Office of the Prime Minister

ጠ/ሚንስትሩን ጨምሮ ማናችንም ከኢትዮጵያ ሕግ በታች ነን፤ ማንም ሰው ከኢትዮጵያ ሕግ በታች ነው

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 31, 2019)፦ ወቅታዊውን የአገሪቱን ሁኔታ አስመልክቶ የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በሠጡት መግለጫ፤ በሰሞኑ ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 78 መኾኑንና ግጭቱን በመቀስቀስ የተጠረጠሩ 409 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ዛሬ ገለጹ። ማንም ሰው ከኢትዮጵያ ሕግ በታች መኾኑንም በመግለጽ መጠየቅ ካለበት ይጠየቃል ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“በጥፋቱ ተሳታፊ የሆኑ ሰዎች ሁሉ በሕግ ተጠያቂነታቸው መረጋገጥ አለበት” ኢሰመኮ

Danile Bekele (PHD), Ethiopian Human Rights Commission

የሰዎች ሕይወት ከመጥፋቱ፣ የአካል ጉዳት ከመድረሱ፣ ንብረት ከመውደሙ፣ … በተጨማሪ፤ ክስተቱ የሕግ የበላይነትን የተፈታተነ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 30, 2019)፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቅርቡ በተከሰቱት ኹከቶች የተሳተፉ አካላቶች በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባ አሳሰበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012፣ 7ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

EZ weekly news digest

ከ67 በላይ ንጹሐን ዜጎችን ሕይወት የቀጠፈው ክስተት ዙሪያ ልዩ ጥንክር

ኢዛ (ከጥቅምት 10 - 16 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በመልካም አላሳለፈችም። ከሳምንቱ መጀመሪያ ጀምሮ የነበረው ድባብ ከወትሮው የተለየ ነበር። ሰዎች በአደባባይ ሞተዋል፣ ቆስለዋል ንብረት ወድሟል። የአገሪቱን ሰላም የሚያናጉ የተለያዩ ተግባራት የተፈፀሙበት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጃዋር መሐመድና አደጋውን ያደረሱ ግለሰቦች ለፍርድ እንዲቀርቡ ኢዜማ ጠየቀ

EZEMA

“ተከብቤአለሁ” በማለት ለደረሰው ጥፋት መነሻ ከኾነው ግለሰብ ጀምሮ አደጋ ያደረሱት በሙሉ ለፍርድ ይቅረቡ! (ኢዜማ)

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 29, 2019)፦ በአገር መረጋጋት፣ ሰላም፣ እንዲሁም ከቀጣሁ ምርጫ ጋር ተያይዞ ባሉ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት በፍጥነት መጀመር እንዳለበት ኢዜማ አሳሰበ። ለሰሞኑ ብጥብጥ፣ የዜጎች ሕይወት መጥፋትና ንብረት መውደም መነሻ ከኾነው ከጃዋር ጀምሮ አደጋው ያደረሱት በሙሉ ለፍርድ ይቅረቡ ሲል ኢዜማ ጠይቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ብሔርንና እምነትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችና ግጭቶች በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ነው” ኢሰመጉ

ETHIOPIAN HUMAN RIGHTS COUNCIL

መንግሥት ሕጋዊና የማያወላውል እርምጃ በመውሰድ የዜጐችን ሕይወትና መብታቸውን ሊያከብረና ሊያስከብር ይገባል!

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 28, 2019)፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባዔ (ኢሰመጉ)፤ “መንግሥት የዜጎችንን ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ይወጣ!” በማለት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ክፍል አንድ አንቀፅ 14ን በመነሻነት ጠቅሶ፤ ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሠሥ፣ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የነፃነት መብት እንዳለው አስታውሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሰሞኑ ብጥብጥ ዙሪያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ከተለያዩ የሕብረተሰብ አካላት ጋር ተወያዩ

PM Dr. Abiy Ahmed

“የኛ ሐሳብ የማይስማማቸው ካሉ አማራጭ ያቅርቡ”

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 28, 2019)፦ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከመከካከያ ሚንስትሩ አቶ ለማ መገርሳና ከኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር በመኾን ከአባገዳዎች፣ ከሃይማኖት አባቶችና ከተለያዩ የሕብረተሰብ ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መምህር ታዬ ቦጋለ መመረዛቸውን ተናገሩ

Taye Bogale

ገዳይ መንጋዎችንና መሰሪ መሪዎቻቸውን የኢትዮጵያ አምላክ እንዴጤዛ ያረግፋቸዋል!

ኢዛ (እሁድ ጥቅምት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 27, 2019)፦ መምህርና የታሪክ ምሁር የኾኑት ታዬ ቦጋለ የተመረዙ መስሎ እንደሚሰማቸው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ትናንት ጠዋት አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚንስትሩ በሰሞኑ ክስተት ከሩሥያ መልስ መግለጫ ሠጡ

ጃዋር መሐመድ

ይህ ሁሉ ለምን እንደመጣብን እናውቃለን፤ ከዚህ የበለጠ ፈተና ቢያጋጥመንም እንኳን የጀመርነውን ጉዞ አናቋርጥም

ኢዛ (ቅዳሜ ጥቅምት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 26, 2019)፦ ሰሞኑን በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች በተፈጠረው እጅግ አሳዛኝ ድርጊቶችን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ማምሻውን መግለጫ ሠጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጃዋርን “ተከብቤአለሁ” የፌስ ቡክ መልእክት ተከትሎ አዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ሐረርና ሌሎች ከተሞች ታምሰው ዋሉ

Young men joined the protest at Jawar's house in the capital Addis Ababa

በአዳማና በሐረር የሰዎች ሕይወት ተቀጠፈ፣ ንብረትም ወደመ

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 23, 2019)፦ በአዲስ አበባ፣ በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልል ከተሞችና በሐረር ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. የተረጋጋ እንቅስቃሴዎችን የሚፈታተን ድባብ ያጠላበት ከመኾኑንም በላይ የሰው ሕይወት የቀጠፈና በንብረት ላይ ውድመት የፈጠረ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ