የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ለ15 ቀን እንዲዘጉ ተወሰነ

ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ

የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመቀነስ ሲባል መኾኑ ተገልጿል

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 18, 2020)፦ በየዕለቱ በአማካይ 18 ሺህ የሚገመቱ ተገልጋዮችን ያስተናግዳሉ የተባሉ ሦስት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመከላከል ሲባል ለ15 ቀናት እንደሚዘጉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫይረሱ ከተገኘባቸው ጋር ንክኪ ያላቸው 922 ሰዎች ክትትል እየተደረገላቸው ነው

Ethiopian Public Health Institute

34 በማቆያ ማዕከል ኾነው ውጤት እየተጠባበቁ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጡት አምስት ግለሰቦች ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው 992 ሰዎች ክትትል እየተደረገባቸው መኾኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ በሠጠው መግለጫ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ በመቀሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን ከፈተ

Prosperity Party

የጽ/ቤቱ ኃላፊም መድቧል “ሕዝቡ ለውጡን ይፈልጋል”

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ በቅርቡ የተቋቋመው የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን መክፈቱን አስታወቀ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ኾነው እንዲሠሩ አቶ ነብዩ ስሑል ሚካኤል ተመድበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተቋረጠው የአገር ውስጥ በረራዎች ቀጠሉ

Ethiopian Airlines

ወደ ደሴ የሚያደረገው በረራ መስተጓጎሉ ተገለጸ

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየር ፀባይ ምክንያት ተስተጓጉሎ የነበረውን የመቀሌ፣ የባህር ዳር፣ የላሊበላ፣ የጐንደር፣ የሁመራ፣ የአክሱምና የሽሬ በረራዎች መልሶ መጀመሩን አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ስድስተኛው የቫይረሱ ተጠቂ ተገኘ

Coronavirus illustration

በጥቆማ በተደረገ ምርመራ በቫይረሱ የተያዘችው እንግሊዛዊት ነች

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባወጣው መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ኮሮና ቫይረስ ያለበት ሰው ተገኝቷል። ቫይረሱ የተገኘባት ስድስተኛዋ ሰው የ59 ዓመት ዕድሜ ያላት እንግሊዛዊት ዲፕሎማት ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ራሳቸውን አግለው የቆዩት ዶክተር ቶላ ከቫይረሱ ነፃ መኾናቸው ታወቀ

ዶክተር ቶላ በሪሶ

ዶክተሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኮሮና ቫይረስ ከተገኘበት ጃፓናዊ ጋር ንክኪ ነበራቸው

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ከተገኘበት ጃፓናዊ ጋር ንክኪ ነበራቸው ተብለው፤ በለይቶ ማቆያ ለብቻቸው ተቀምጠው የነበሩት የኦሮሚያ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ፤ ከቫይረሱ ነፃ መኾናቸው ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 27ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 27th, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሃያ ሰባተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከየካቲት 30 - መጋቢት 6 ቀን 2012 ዓ.ም.):- ሳምንቱ እንዴት ሰነበተ? የሚል ጥያቄ ከተነሣ ከየትኛውም ክስተትና ድርጊት በላይ የኮሮና ቫይረስ በአንድ የ48 ዓመት ጐልማሳ ጃፓናዊ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን የሚገልጸው ዜና ለኢትዮጵያ የሳምንቱ ዐቢይ ጉዳይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኮሮና ምክንያት ብሔራዊ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለ15 ቀናት እንደሚዘጋ ተገለጸ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነገውን ስብሰባ ሰረዘ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ያካሒድ የነበረውን ስብሰባ ሰረዘ

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ ብሔራዊ ሙዚየም ለቀጣዮቹ አሥራ አምስት ቀናት ዝግ እንደሚኾን የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በነገው ዕለት ሊያካሒደው የነበረውን መደበኛ ስብሰባ ሰርዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መመሪያ ተላለፈ

Prof. Hirut Woldemariam

ለ45 ዩኒቨርሲቲዎች መመሪያው ተላልፏል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ሁሉም የመንግሥትና የግል ከፍተኛ ተቋማት ሊተግብሯቸው ይገባል ያሉትን መመሪያ አስተላለፉ። ይህ መመሪያ እንዲደርሳቸው የተደረጉት 45 ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ቫይረስ ምርመር ላለማድረግ ያመለጠው ግለሰብ ከቫይረሱ ነፃ ኾነ

Wello

አምልጦ ደቡብ ወሎ ላይ ነበር የተያዘው

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች በማሳየቱ ተጨማሪ ምርመራ ሊደረግለት ሲል፤ አምልጦ ደቡብ ወሎ ላይ የተያዘው ግለሰብ የምርመራ ውጤት ከቫይረሱ ነፃ መኾኑን አመለከተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ