በጀርመን ፍራንክፈርት የሻማ ማብራት ሥነሥርዓትና የፊርማ ማሰባሰብ ተካሄደ

Frankfurt candlelight vigil and petition

Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም ፲፮ ቀን ፪፲፻፱ ዓ.ም. September 26, 2016)፦ በኢትዮጵያ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ/ኢህአዴግ መንግሥት በኦሮሞ፣ በአማራና በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ውስጥ እየወሰደ ያለውን የመግደል፣ የማሰቃየትና የማሰር ተግባር በመቃወም፤ በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ቅዳሜ መስከረም ፲፬ ቀን ፪፲፻፱ ዓ.ም. ዕለት የሻማ ማብራት ሥነሥርዓት ተካሄደ። ይኸው ሥነሥርዓት የጀርመንዋ መሪ አንጌላ መርክል በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ጉዞ እንዲሰርዙ የሚጠይቅ የፊርማ ማሰባሰብን ያካተተ እንደነበር ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፕ/ር ፍቅር ቶሎሳ ”የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” መጽሐፍ በድሬዳዋ ተመረቀ

“መጽሐፉ ሠላምና ፍቅርን የሚሰብክ፤ ወደ አንድነት እንድንመጣ የሚረዳን ነው” ፀሐፊና ጋዜጠኛ ገነት አየለ

“መጽሐፉ ባለፉት 25 ዓመታት አማራና ኦሮሞን ለማራራቅ ሲጥሩ የነበሩ ፀረ-አንድነት ኃይሎችን አንገት ያስደፋ ነው” አስተያየት ሰጭዎች

Prof. Fikre Tolossa signing his new book in Dire Dawa, 11th Aug. 2016.

Ethiopia Zare (ሰኞ ነሐሴ 16 ቀን 2008 ዓ.ም. August 22, 2016):- በቅርቡ ”የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” በሚል ርዕስ አዲስ መጽሐፍ ያሳተሙት ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ፤ በድሬዳዋ ከተማ ትናንት እሁድ ነኀሴ 15 ቀን 2008 ዓ.ም. በኤምኤ ሆቴል ከአካባቢው ነዋሪዎችና ታዋቂ ሰዎች ጋር የመጽሐፍ ንባብ፣ ውይይት እና የፊርማ ሥነሥርዓት አካሄዱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የፍርሃት ከፈን፤ በጎንደር ተቀደደ፤ የጎሕ ብርሃን በኢትዮጵያ ፈነጠቀ!” ጎሕ

የጎንደር ሕብረት / GOHEthiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 27 ቀን 2008 ዓ.ም. August 3, 2016):- ”የጎንደር ሕብረት” ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኦገስት 2 ቀን 2016 እ.ኤ.አ.)፤ ”የፍርሃት ከፈን፤ በጎንደር ተቀደደ፤ የጎሕ ብርሃን በኢትዮጵያ ፈነጠቀ!” በሚል ርዕስ ያወጣውን ልዩ መግለጫ ለኢትዮጵያ ዛሬ ልኳል። መግለጫው በህወሓት የሚመራው ገዥ ፓርቲን አፈና፣ ጭቆናና በደል የመረረው ህዝብ፤ በተለይ ባላፈው እሁድ ሐምሌ 24 ቀን በጎንደር ከተማ ላይ ህዝባዊው ኃይል የነበረውን የጨለማ ዘመን ገፍፎ መውጣቱን አመላካች መሆኑን ጠቁሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከሆላንድ የገባውን ዲያስፖራ ስምንት ቦታ በሳንጃ የገደሉት አልተያዙም

ለይኩን እሸቱ. Leyikun Eshetu(ኢ.ኤም.ኤፍ) ከሚኖርበት ሆላንድ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ የገባው ወጣት ለይኩን እሸቱ፤ በፋሲካ በዓል ዋዜማ ስምንት ቦታ በስለት ወግተው የገደሉት ወንጀለኞች እስካሁን አልተያዙም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ ገዳዮቹ ባለጊዜዎች ስለሆኑ ሟች ደመ ከልብ ሆኖ ቀርቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግዕዝ ፊደል የዩናይትድ ስቴትስ የባለቤትነት መብት አገኘ

Geezedit. ግዕዝኤዲት

ዋና መሥሪያ ቤቱ ብራይተን ኮሎራዶ የሆነው የኢትዮጵያ ኮምፕዩተሮችና ሶፍትዌር ቁጥሩ ዘጠኝ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ኃምሳ ሰባት የሆነ የዩናይትድ ስቴትስ የባለቤትነት መታወቂያ (ፓተንት) መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም. (አፕሪል 7 ቀን 2016 እ.ኤ.አ.) ማግኘቱን አስታወቀ። ፓተንቱ የተሰጠው ለፈጠራውና የኩባንያው ባለቤት ለዶ/ር አበራ ሞላ ሲሆን፤ ኩባንያው የእርሳቸውንና የባለቤታቸው የወ/ሮ ሠናይት ከተማ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንጋፋው የሳክስፎን ተጫዋች አርቲስት ጌታቸው መኩሪያ አረፈ

Artist Getachew Mekuria. አርቲስት ጌታቸው መኩሪያ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 26 ቀን 2008 ዓ.ም. April 4, 2016):- በ1927 ዓ.ም. የተወለደው አርቲስት ጌታቸው መኩሪያ ጥበብን የተቀላቀላት በመንገድ ላይ ታንቡር መቺ በመሆን ነው። ይህ የሆነው በ1940 ዓ.ም. ነበር ። በኋላም ጥበብን እየተከተላት እሷም ወዳለችበት እየጠራችው በ1948 ዓ.ም. በመዘጋጃ ቤት ተቀጥሮ በፊት ከሚያደንቃቸው በኋላም ለረጅም ዓመታት አብረውት ከሠሩት ከአርቲስት ተፈራ አቡነወልድና ከአርቲስት ወዳጄነህ ፍልፍሉ ጋር ተቀላቀለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ኮንቴይነር የተጫነ ሰው ስዊድን ተገኘ

ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን የሚያሸጋግሩ አሉ ብሎ ይጠረጥራል

Ethiopian Airlines 787 dreamliner የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን (Foto: STEFAN MATTSSON)

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. Mar. 01, 2016)፡- ከአዲስ አበባ ሌሊት ተነስቶ ዛሬ ጠዋት በስዊድን መናገሻ ስቶክሆልም በሚገኘው የአርላንዳ አየር ማረፊያ ባረፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን የዕቃ ኮንቴይነር ውስጥ የተደበቀ የ27 ዓመት ዕድሜ ያለው አንድ ሰው መገኘቱን ፖሊስ ገለጸ። ይኸው ግለሰብ በስዊድን ጥገኝነት መጠየቁ ታውቋል። ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎች የሚያሸጋግሩ ወገኖች እንዳሉ ጥርጣሬ አለኝ፣ ጉዳዩን እያጣራኹ ነው አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ድረገጽ ተጠለፈ

Anon+

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓ.ም. Feb. 08, 2016)፡- በኢህአዴግ መንግሥት ሙሉ ቁጥጥር ስር ያለውና ጋዜጦችንና መጽሔቶችን የሚያሳመው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ድረገጽ “አኖን ፕላስ” (AnonPlus) በተሰኙ ያልታወቁ ወገኖች ከቅዳሜ ጥር 28 ቀን ጀምሮ ተጠለፈ (ሐክ ተደረገ)። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ ድረገጹ እንደማይሠራ ለመገንዘብ ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመጀመሪያው በግዕዝ ፊደል የሚጽፍ ኮምፒዩተር ገበያ ላይ ዋለ

ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፊደል በላፕቶፕና በዲስክቶፕ ተቀርጾ አገልግሎት መስጠት ቻለ

The first Amharic, Geez laptop

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓ.ም. January 15, 2016)፡- ጋዜጠኛና ፀሐፊ ገነት አየለ የኢትዮጵያ ፊደላት እንደሌሎቹ የቋንቋ ፊደላት በላፕቶፕና በዴስክቶፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀርጸው ለተጠቃሚዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ መቻላቸውን ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል። ይኸው የመጀመሪያው በኢትዮጵያ ፊደል የሚጽፍ ኮምፒዩተር በገበያ ላይ መዋሉ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰብዓዊ መብት ቀን በፍራንክፈርት ተከበረ

ዮሐንስ ደሳለኝ (ጀርመን - ፍራንክፈርት)

የሰብዓዊ መብት ቀን በፍራንክፈርት ተከበረ

በየዓመቱ ዲሰምበር 10 የሚከበረው የሰብዓዊ መብት ቀን ሐሙስ December 10,2015 በፍራንክፈርት የዋናው ባቡር ጣቢያ አካባቢ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ አመሸ። ከተለያዩ አገሮች የመጡ ተገን ጠያቂዎች የተገኙበት ይህ አከባበር ለየት ያለና የወቅቱ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚገባው ብርድ ያልበገረው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ