Home ዜና አና ጐሜዝ የአውሮፓ ሕብረት መሪዎችን ወቀሱ
አና ጐሜዝ የአውሮፓ ሕብረት መሪዎችን ወቀሱ PDF Print E-mail
Friday, 18 July 2008 11:31

Anna GomezEthiopia Zare (ዓርብ ሐምሌ 11 ቀን 2000 ዓ.ም. July 18, 2008)፦ የአውሮፓ ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አባልና ዲፕሎማት የሆኑት ሚስ አና ጐሜዝ የአውሮፓ ሕብረት መሪዎች በቡድን 8 ሀገሮች ጉባዔ ላይ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ከሚወቀሱ የአፍሪካ መሪዎች ጋር መሆን ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ ያላቸው አመለካከት ዝቅተኛ ነው በማለት ወቀሱ።

 

አና ጐሚዝ ዩሮ አክቲቭ ከተባለ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ እንደገለፁት በቡድን 8 ስብሰባ ላይ ሁሉም መሪዎች በዚምባቡዌ ላይ ማዕቀብ ለመጣል ፍላጐታቸውን በሚያሳዩበት ወቅት፣ በዚያው አንፃር በስብሰባው ላይ በሰብአዊ መብት ረገጣ የሚወነጀሉት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በጉባዔው ላይ እንዲካፈሉ በማድረግ ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ ያላቸውን ምልከታ የተዛባ መሆኑን አሳይተዋል ብለዋል።

 

በቶኪዮ የግሩፕ 8 ስብሰባ ላይ ከአውሮፓ ሕብረት ከፍተኛ ባለሥልጣኖች መካከል ኮሚሽነሩ ባሮስ በተገኙበት ፕሮግራም የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ከሀገር ሀገር ለያይተው ማየታቸው፣ ሁሉንም መሪዎች በሰብዓዊ መብት ጉዳይ ደካማ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ብለዋል። 

 

 
 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ