Home ዜና አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሩን መረጠ
አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሩን መረጠ PDF Print E-mail
Wednesday, 18 June 2008 09:52

ወ/ት ብርቱካን የድርጅቱ ሊቀመንበር ሆና ተመረጠች

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 11 ቀን 2000 ዓ.ም. June 18 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳን የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መሾሙ ታወቀ።

 

ድርጅቱ አራት የምክትል ሊቃነመናብርት የመረጠ ሲሆን፣ የድርጅት ጉዳይና ምክትል ሊቀመንበር ኢንጂንየር ግዛቸው ሽፈራሁ፣ የውጭ ጉዳይና ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም፣ የህዝብ ግንኙነትንና ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ፣ የፋይናንስና የአስተዳደር እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር አቶ ተመስገን ዘውዴ፣ የተመረጡ ሲሆን፣ አቶ አስራት ጣሴን የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ በማድረግ የሾመ መሆኑ ታውቋል።

 

 
 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ