Home ዜና የአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ ለሰኔ ሰባት ተዛወረ
የአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ ለሰኔ ሰባት ተዛወረ PDF Print E-mail
Sunday, 25 May 2008 00:25

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 17 ቀን 2000 ዓ.ም. May 25, 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. ሊያደርገው የነበረውን ጠቅላላ ጉባዔ ለሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. ማዛወሩን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

 

እሁድ ግንቦት 10 ቀን የላዕላይ ምክር ቤቱ ባደረገው ስብሰባ ጠቅላላ ጉባዔው ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. እንዲጠራ መወሰኑን መዘገባችን አይዘነጋም። እንደ ኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጻ ከሆነ ጉባዔው ሊራዘም የቻለው ጠቅላላ ጉባዔው ሊካሄድበት ታቅዶ ከነበረው የሆቴል አዳራሽ ጋር በተያያዘ ችግር ምክንያት ነው።

 

እስካሁን ድረስ ከምርጫ ቦርድ ሕጋዊ ፈቃድ ለማግኘት ማመልከቻ ያላስገባውና በወ/ት ብርቱካን የሚመራው የቀድሞው የቅንጅት ፓርቲ፣ የአሁኑ የ”አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ” በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የድርጅቱን አመራሮች እንደሚመርጥ መዘገባችን አይዘነጋም።

 

ጠቅላላ ጉባዔው ተካሂዶ ካበቃ በኋላ ፓርቲው ሕጋዊ ፈቃድ ይሰጠው ዘንድ ለምርጫ ቦርድ ማመልከቻውን ያስገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ መዘገባችን ይታወሳል።

 

ተያያዥ

 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ