Home ዜና አንድነት ግንቦት 23 ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሂዳል
አንድነት ግንቦት 23 ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሂዳል PDF Print E-mail
Monday, 19 May 2008 12:48

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2000 ዓ.ም. May 19, 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ትናንት ባካሄደው የላዕላይ ምክር ቤት ስብሰባው ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔውን ለመጥራት መወሰኑን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ወገኖች ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጡ።

 

እስካሁን ድረስ ከምርጫ ቦርድ ሕጋዊ ፈቃድ ለማግኘት ማመልከቻ ያላስገባውና በወ/ት ብርቱካን የሚመራው የቀድሞው የቅንጅት ፓርቲ፣ የአሁኑ የ”አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ” ግንቦት 23 በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የድርጅቱን አመራሮች እንደሚመርጥ ይጠበቃል።

 

ጠቅላላ ጉባዔው ተካሂዶ ካበቃ በኋላ ፓርቲው ሕጋዊ ፈቃድ ይሰጠው ዘንድ ለምርጫ ቦርድ ማመልከቻውን ያስገባል ተብሎ ይጠበቃል።

 

ተያያዥ

 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ