ዜና - News
በሲያትል ለኢሳት 50ሺህ ዶላር ተሰበሰበ
የጋዜጠኞቹ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት አለሙና ውብሸት ታዬ ምስል 33ሺህ ዶላር በጨረታ ተወስዷል
Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዚያ 14ቀን 2005 ዓ.ም. April 22, 2013)፦ ትላንት ምሽት በሲያትል ከተማ የኢሳትን ሶስተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ አርቲስትና የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው ታማኝ በየነ እና አቶ መንሱር ኑር በክብር እንግድነት የተገኙበት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ምሽት ላይ 50ሺህ የአሜሪካን ዶላር መሰብሰቡ ታወቀ።
በቤንች ማጂ አማርኛ ተናጋሪዎችን ማፈናቀል ዳግም ተጀመረ
(ፍኖተ ነፃነት ቁ. 71፣ መጋቢት 29 ቀን 2005)፦ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን በሚገኘው ሜኒት ወልድያ ወረዳ በተለይም ዘንባብና አርፋጅ ቀበሌ ነዋሪዎች በካከል ከ350 በላይ የአማርኛ ተናጋሪ ዜጎች ተፈናቅለው በወረዳው አካባቢ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
የፋሽስቱ ግራዚያኒን ሐውልት መሠራት ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ የወጡ በአ.አ. ታሰሩ
”ይህ የጤንነት አይመስለኝም!” ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም
Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. March 17, 2013)፦ የፋሽስቱን ግራዚያኒ ሐውልት በጣሊያን ሀገር በመሠራት ላይ መሆኑን በመቃወም በአዲስ አበባ ሰልፍ ለማድረግ የወጡ ከ35 በላይ ኢትዮጵያውያን ታሰሩ። ከእነዚህም ውስጥ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም፣ አቶ ታዲዮስ ታንቱ፣ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ይልቃል ጌትነት ጨምሮ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አመራር አባላት በዛሬው ዕለት ታስረዋል።
"ከእኔ ልጅ ጋር ሐረር ከተማ ውስጥ አራት ሰው በፓሊስ ነዳጅ እየተደፋበት በእሳት ተቃጥሎ ሞቷል"
ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ (ከሐረር የሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈፅሞባቸው የተባረሩ አዛውንት)
ፍኖተ ነፃነት (መጋቢት 7 ቀን 2005 ዓ.ም.)፦ "ልጄ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት ተደርጋ፣ ቤቴን ተነጥቄና ንብረቴ ወድሞ ከሐረር ተባረርኩ" ሲሉ አንዲት የ67 አመት ባልቴት በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አስታወቁ።
"የህወሓት/ኢህአዴግ የውስጥ ፍጥጫ፣ ዴሞክራሲን አይወልድም" ሸንጎ
Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 27 ቀን 2005 ዓ.ም. March 6, 2013)፦ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች (ህወሓት፣ ኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴን) አባላት ጅርጅታቸው ለረጅም ጊዜ ከተዘፈቁበት አረንቋ ውስጥ በማውጣት የሀገራችንን ክብርና የህዝባችንን መብት ያረጋገጠ መሠረታዊ ለውጥ እንዲመጣ ይታገሉ ዘንድ ሸንጎ መጠየቁን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው መግለጫ አስታወቀ።
አርቲስት በኃይሉ መንገሻ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
አለምፀሐይ ወዳጆ
በኢትዮጵያ የትያትር ሙያ ተደናቂና ተወዳጅ የነበረው አርቲስት በኃይሉ መንገሻ በተወለደ በ57 ዓመቱ ማርች 3/2013 (የካቲት 24/2005) ዓ.ም. ነዋሪ ሆኖ በቆየበት በሰሜን አሜሪካ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
በፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ቆንስላ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ

ዳዊት ፋንታ
ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ400 በላይ የሚሆኑ እ.ኤ.አ. በማርች 01 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍራንክፈርት በሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ፊት ለፊት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ።
በስዊድን የስደተኞች ማኅበር ከስደተኞች ጉዳይ አጥኚ ተወካዮች ጋር ውይይት አደረገ
Ethiopia Zare(እሁድ የካቲት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. February 23, 2013)፦ በስዊድን የሚገኘው የኢትዮጵያ ስደተኞች ማኅበር የኢትዮጵያን ጉዳይ ከሚከታተሉ የኢሚግሬሽን ተወካዮች ጋር ፌብሪዋሪ 6 ቀን 2013 ዓ.ም ውይይት አደረገ። ይህንኑም ጉዳይ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ እስር ቤት ከርመው የተፈቱት ጋዜጠኞች ማርቲን ሼቢ እና ዮሃን ፐርሾን ለኢሚግሬሽን ባለስልጣናት እንዳስረዱ አቶ ፋንታሁን ገልጸዋል።
በጅሃዳዊ ሐረካታ ፊልም ላይ ከ33ቱ ፔቲሽን ፈራሚዎች የተሰጠ መግለጫ
Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 7 ቀን 2005 ዓ.ም. February 14, 2013)፦ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በተከታታይ ያሳየውን ”ጅሃዳዊ ሐረካት” የተሰኘ ፊልም አስመልክቶ፤ ሰላሳ ሦስቱ ፔቲሽን ፈራሚዎች ባወጡት መግለጫ ”ለዘመናት በፍቅርና መከባበር የኖረን ህዝብ በደረቅ ፕሮፓጋንዳ መነጣጠልና መከፋፈልም ሆነ የመብት ጥያቄውን ማዳፈን አይቻልም!” በማለት በፊልሙ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ገልጸዋል።
ኦስሎ በታማኝ በየነ ደምቃ አመሽች
ሔለን ዘውዱ
የኢሳት ኖርዌይ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ዕሑድ የካቲት 3 ቀን 2005 ዓ.ም. (ፌብሩዋሪ 10 ቀን 2013 እ.ኤ.አ.) በዋና ከተማዋ በኦስሎ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።

