|
Thursday, 24 July 2008 13:49 |
|
Ethiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ለታዋቂው ኢትዮጵያዊ የሥነ ጥበብ አባት ለሎሬት ፀጋዬ ገብረመድኅን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በመጀመሪያ ስሙ መጠሪያ ”ፀጋዬ” የተሰኘ ድረ ገጽ መከፈቱንና በይፋ ሥራውን መጀመሩን ድረ ገጹ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው ኢ-ሜይል ገለጸ።
|
|
Read more...
|
|
Thursday, 24 July 2008 13:31 |
|
ስሙን በሚመለከት ማሻሻያ ሳያደርግ ቦርዱ እንዲወስንለት ጠየቀ Ethiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ”አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ” ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ ፈቃድ መጠየቂያ ማመልከቻ ካስገባ በኋላ፤ ባለፈው ሣምንት ኀሙስ ዕለት ምርጫ ቦርድ በጽ/ቤቱ በኩል አስር ነጥቦችን ዘርዝሮ ማሻሻያዎችና ለውጦች እንዲደረግባቸው ለፓርቲው በደብዳቤ አሳውቆ በነበረው መሠረት፣ ፓርቲው በዛሬው ዕለት በደብዳቤ ምላሽ መስጠቱን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ። |
|
Read more...
|
|
Wednesday, 23 July 2008 17:16 |
|
Ethiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ቴዲ አፍሮን ፖሊሶች ሲጎትቱት የሚያሳየውን ፎቶግራፍ (በግራ በኩል የሚታየውን ፎቶ) በፊት ገጹ ላይ ያወጣው በሀገር ውስጥ የሚታተመው ”መሰናዘሪያ” የተባለው ጋዜጣ በፎቶግራፉ ምክንያት መከሰሱን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው መረጃ አስረዳ። የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ወሰንሰገድ መሸሻን ፖሊስ ጠርቶታል።
|
|
Read more...
|
|
Wednesday, 23 July 2008 12:04 |
|
በመኢአድ ስም ሊቀጥሉ ይችላሉ
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የቅንጅት አመራሮች ከእስር ከተፈቱ በኋላ በተፈጠረው ልዩነት ኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመሩት ቡድን ”ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ” ይገባኛል በማለት ምርጫ ቦርድን ከስሶ ሲከራከር የነበረ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት የዋለው ችሎት ለምርጫ ቦርድ ወስኖ እነኢ/ር ኃይሉ ሻውልን ”ቅንጅት” የሚለውን ስም መከልከሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው መረጃ ጠቆመ። |
|
Read more...
|
|
Tuesday, 22 July 2008 12:15 |
|
የታሰሩት “ችሎት ረብሻችኋል፣ ድንጋይ ወርውራችኋል” በሚል ነው
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ በትናትናው ዕለት የቴዲ አፍሮን ችሎት ለመከታተል ከመጡ ችሎት ተከታታዮች መካከል አስሩ ታሰሩ። በዛሬው ዕለትም ፖሊስ ሜክሲኮ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ነክ ፍርድ ቤት አምስቱን አቅርቧቸው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀባቸው ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ፈቅዶለታል። |
|
Read more...
|
|
Tuesday, 22 July 2008 03:57 |
|
የእነ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ሥራ አስኪያጅ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የፊታችን ነሐሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. (August 8, 2008) በሚከፈተው የቤጂንጉ ኦሎምፒክ የሚሳተፉ አትዮጵያውያን አትሌቶች ታወቁ። በዚህ በቻይና በሚደረገውና 17 ቀናት በቀሩት ኦሎምፒክ ላይ ኢትዮጵያ በአምስት የተለያዩ ውድድሮች በሴቶችም በወንዶችም ትሳተፋለች። |
|
Read more...
|
|
Monday, 21 July 2008 06:29 |
|
- ክሱን ተከላከል ተባለ
- ወዳጅ ዘመዶቹ በእንባ ተራጭተዋል Ethiopia Zare (ሰኞ ሐምሌ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. July 21, 2008)፦ አዲስ አበባ በፍተኛ ዝናብ ተውጣለች። ዝናቡን ከምንም ያልቆጠሩ የቴዲ አፍሮ ቤተሰቦች፣ ጓደኞችና አድናቂዎቹ በከፍተኛው ፍርድ ቤት መግቢያ በር ላይ በተለመደው ሁኔታ ሰልፍ ይዘዋል። ከላይ ስለሚወርድባቸው ዝናብ አንድም ያዘነ ፖሊስ አለነበረም። “ምናለበት ውስጥ ገብተን ብንጠብቅ?” የሚለው ጥያቄም መልስ አላገኘም። በተለመደው ሰዓት ከጠዋቱ 2፡45 ሲሆን፣ ወደ ግቢው እንድንገባ ተፈቀደ። |
|
Read more...
|
|
Monday, 21 July 2008 04:18 |
|
”እንደትናንቱ ሁሉ ዛሬም አብራችሁን እንድትሆኑ እጠይቃለሁ” አቶ አስራት ጣሴ ”ለአኝዋክ ህዝብ ብቻ መታገል መፍትሔ አያመጣም” አቶ ኦባንግ ሜቶ ”በዓለም ላይ ካሉ ሀገሮች ምንም ሥራ የማይሠራው የአቶ መለስ ዜናዊ መንግሥት ብቻ ነው” ፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም ”ኢትዮጵያዊነታችሁ የማትገላገሉት ስለሆነ የምትኮሩባት ኢትዮጵያ እንድትሆን መታገል አለባችሁ” ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም 
Ethiopia Zare (ሰኞ ሐምሌ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. July 21, 2008)፦ ትናንት እሁድ ሐምሌ 13 ቀን 2000 ዓ.ም. አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ በሲያትል ከህዝብ ጋር ያደረገው ውይይት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ታወቀ። በዚህ ህዝባዊ ውይይት ላይ ተጋባዥ ተናጋሪዎች የነበሩት ፕ/ር መስፍን ወልደማርያምና አቶ አስራት ጣሴ ከአንድነት ፓርቲ፣ ፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም እና አቶ ኦባንግ ሞቶ ናቸው። |
|
Read more...
|
|
Sunday, 20 July 2008 23:41 |
|
Ethiopia Zare (ሰኞ ሐምሌ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. July 21, 2008)፦ የብዙዎችን ቀልብ ገዝቶ የቆየው ታዋቂውና ተወዳጁ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ከሦስት ወራት የእስር ቆይታ በኋላ በአወዛጋቢው የምኒልክ ሆስፒታል የሰነድ ማስረጃ የዓቃቤ ሕግ ክርክር ተደምድሟል። ፍርድ ቤቱም በዛሬው ችሎቱ በጉዳዩ ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል። |
|
Read more...
|
|
Saturday, 19 July 2008 11:02 |
|
የፍ/ቤቱ ትዕዛዝ 15 ቀን ቢሆነውም እስካሁን አልቀረቡም መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን በሰበር አሳግዷል Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሐምሌ 12 ቀን 2000 ዓ.ም. July 19, 2008)፦ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ባለሥልጣን ሥራ አስኪያጅን ፖሊስ አስሮ እንዲያቀርባቸው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ። |
|
Read more...
|
|
|
|
|
|
Page 1 of 20 |