Home ቃለምልልስ Interview በቅንጅት ስም የተሰበሰበው ገንዘብ የማነው?
በቅንጅት ስም የተሰበሰበው ገንዘብ የማነው? Print E-mail
User Rating: / 12
PoorBest 
Interview
Wednesday, 23 July 2008 11:10

ድጋፍ አሰባሳቢዎቹ መልስ አላቸው

በኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመራው ቡድን ቅዳሜ ሰኔ 13 ቀን እና እሁድ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔ አድርጎ አመራሮቹን መምረጡ አይዘነጋም። በጠቅላላው ጉባዔ ም/ፕሬዝዳንትና የሰሜን ኢትዮጵያ ቀጠና ኃላፊ ሆነው የተመረጡት አቶ አባይነህ ብርሃኑ፤ የጉባዔው መዝጊያ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠታቸውን መዘገባችን አይዘነጋም።

 

በዕለቱ የቀድሞው የቅንጅት አመራሮች ከእስር ከመፈታታቸውም ሆነ ከተፈቱ በኋላ በውጭ አገር የሚገኙ ቻፕተሮች ያሰባሰቡት ገንዘብ በቅንጅት ስም በመሆኑ ሊመልሱላቸው እንደሚገባ አቶ አባይነህ አምርረው ተናግረዋል። ይህ ካልሆነ ግን ጉዳዩን ወደ ሕግ በመውሰድ ገንዘቡን ገቢ እንደሚያደርጉም ዝተው እንደነበር መዘገባችን አይዘነጋም።

 

ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ከቅንጅት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ አሰባሳቢ ማኅበር ሊቀመንበር የሆኑትን አቶ አክሎግ ልመንህን፣ በካናዳ የቻፕተሮቹ አስተባባሪ አቶ ዮሱፍ ዑመርን፣ እንዲሁም ከአውሮፓ የስዊድኑን ሊቀመንበር አቶ ታምራት አዳሙን እንቢልታ ጋዜጣ በቅጽ 1፣ ቁጥር 27 ዕትሙ ስለጉዳዩ አነጋግሯቸዋል። ሙሉውን ዘገባ በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!

 

 
 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ