በፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ቆንስላ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ

ዳዊት ፋንታ
ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ400 በላይ የሚሆኑ እ.ኤ.አ. በማርች 01 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍራንክፈርት በሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ፊት ለፊት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ።
በአባይ ግድብ ዙሪያ
ግርማ ካሳ
ቋጠሮ የተሰኘ ድረ ገጽ ላይ የወጣ አንድ ቪዲዮ አየሁ። በሪያድ ሳውዲ አረቢያ፣ የኢሕአዴግ ባለስልጣናት፣ ኢትዮጵያውያንን ጠርተው፣ በአባይ ግድብ ዙሪያ ባነጋገሩበት ወቅት፣ የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ቪዲዮ ነው። «መብትን መጠየቅ አሸባሪነት አይደለም»፣ «የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 27 ይከበር» የሚሉ መፈክሮች የተጻፉባቸው ነጭ ወረቀቶች ሲውለበለቡ ይታያሉ። ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ የተካሄደ፣ ለአባይ ግንባታም በቂ ገንዘብ የተሰበሰበ አይመስልም።
የህወሓት ፍጥጫ ቀጥሏል
"አሁን ያለው ህወሓት ቆዳ ነው" እነ ስብሃት
"የህወሓት ወራሾች እኛ ነን" እነ አባይና አዜብ
ኢየሩሳሌም አርኣያ
ሁለት ቦታ የተከፈለው የህወሓት አመራር ልዩነቱን በማስፋት እየተወዛገበ መሆኑን ከመቀሌ ታማኝ ምንጮች ገለፁ። ስብሃት እና አዜብ የሚመሩት ሁለቱ ቡድን አነጋጋሪ አቋም ይዞ መውጣቱን ምንጮቹ ጠቁመዋል። በስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድን ባስቀመጠው አቋም "መለስ ህወሓትን ገድሎ ነው የሔደው! አሁን ያለው ህወሓት ቆዳ ነው።
የፍርሃትና ስም ማጥፋት ፖለቲካ በኢትዮጵያ
ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሃገሬ)
2011፡ የሙስና አገዛዝ፤ ፍርሃትና ስም ማጥፋት
በዲሴምበር 2011 "ኢትዮጵያ የደም ሃገር ወይም የንቅዘት (ሙስና) ሃገር" በሚል ርእስ የኢትዮጵያን ሁለት ገጽታ በማመዛዘን አንድ ጦማር አስነብቤ ነበር። በዚያን ወቅት ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በተባለው ተቋም ተቀምጦ የነበረው ገጽታ ያሳየው ኢትዮጵያ ለም መሬቶች በተንኮል በተጠቀለለ ስውር ደባ እየተቸበቸቡ እንደነበር ነው።
ወያኔና እምነት
ቸሩ ላቀው
በመንግሥት አመራር ላይ የተቀመጡ ቡድኖችና በኃይማኖት አመራር ላይም የተቀመጡ የኃይማኖት መሪዎች በየፊናቸው የሕዝብን አደራ በኃላፊነት ተቀብለው በሀገሪቱ ባለው ሕገ መንግሥትና በኃይማኖቱ ሕግ መሠረት በሐቅና ለሕቅ ብለው ምለውና ተገዝተው ሕዝብን ለማገልገል የተቀመጡ ናቸው።
የሚሳናቸው የለም
ቸሩ ላቀው
ሿሚ፣ ሻሪ፣ ሀገር መከፋፈልና መገነጣጠል የነርሱ ተግባር ሆኗል። መለስን ሾሙብን፣ ሀገርን ገንጥለው ኢሳያስ አፈወርቂን ኤርትራን ይዘህ ራስህን ቻል አሉት። ከመለስ ሹመት ጋር ኢትዮጵያን በጎሣ ከፋፍለው እያወደሟትና እያደቀቋት ነው።
በስዊድን የስደተኞች ማኅበር ከስደተኞች ጉዳይ አጥኚ ተወካዮች ጋር ውይይት አደረገ
Ethiopia Zare(እሁድ የካቲት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. February 23, 2013)፦ በስዊድን የሚገኘው የኢትዮጵያ ስደተኞች ማኅበር የኢትዮጵያን ጉዳይ ከሚከታተሉ የኢሚግሬሽን ተወካዮች ጋር ፌብሪዋሪ 6 ቀን 2013 ዓ.ም ውይይት አደረገ። ይህንኑም ጉዳይ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ እስር ቤት ከርመው የተፈቱት ጋዜጠኞች ማርቲን ሼቢ እና ዮሃን ፐርሾን ለኢሚግሬሽን ባለስልጣናት እንዳስረዱ አቶ ፋንታሁን ገልጸዋል።
አስሩ የጽልመት ቀናት በኢትዮጵያ
(ከየካቲት 8/1929 - የካቲት 17/1929 ዓ.ም)
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንን ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር።
ወላጆችና መሪዎች
ቸሩ ላቀው
ለዚህ የተቀደሰ ተግባርና ከባድ ኃላፊነትን ለሚጠይቅ ሥልጣን መታጨት ያለባቸው የሀገር መሪዎች ማሟላት ያለባቸው መመዘኛዎች በርካቶች ቢሆኑም በኔ እይታ አንዳንዶቹን ከወላጆች ጋር እያስተያየሁ ለመጠቃቀስ እፈልጋለሁ።
ድንቄም ምርጫ!
ይኸነው አንተሁነኝ
ላንዲት ሀገር መሰረታዊ የእድገት ኃይል ያላት የተፈጥሮ ሃብትና የሕዝቦቿ ሁለንተናዊ ብቃት ናቸው። የሕዝቦቿን ሁለንተናዊ ብቃት ለመገንባት ደግሞ ካሏት የትምህርት ተቋማትና የትምህርቱ ሥርዓት በተጨማሪ በሕዝቦቿ መካከል ያለው የባህል፣ የኃይማኖትና የአኗኗር መስተጋብር የሚያበረክቱት አስተዋጽኦና በዚሁ ሳቢያም የሚገኘው ቀጥተኛ ያልሆነ የእውቀትና የልምድ አቅምና ዝውውሩ የሚናቅ አይሆንም።
