በታዳጊ ወጣቶች ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ ችግሮችን ለማስወገድ የታሰበ መድረክ ተዘጋጀ
በ17 ዓመቷ ራሷን ያጠፋችው ወጣት ቤተሰቦች ልምድ ያካፍላሉ!
“በእኔ ቤተሰብ የደረሰ ልብ የሚሰብር ሀዘን በሌሎች ወገኖቼ ላይ ደርሶ ማየት አልፈልግም” (የኤደን ወላጅ አባት)
‘ልጄን እንደ ንግስት ነበር ያሳደኳት፤ የዚህ ሀገር ልጅ ምኑም አይታወቅም” የኤደን እናት ወ/ሮ በለጡ
ደራሲ ሐምራዊት ተስፋ በውይይቱ ላይ ትናገራለች!
የአማንዳ ቶድ ወላጅ እናት በውይይቱ ተካፋይ ናቸው!
Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 5ቀን 2005 ዓ.ም. May 13, 2012)፦ ባለፈው መስከረም 24 ቀን 2012 ዓ.ም በቫንኩቨር ካናዳ ህይወቷን ያጣችው የ17 ዓመት ታዳጊ ወጣት ኤደን ዘውዱ ቤተሰቦች በራሳቸው ቤተሰብ የደረሰ ሀዘን በሌሎች ወገኖች ላይ እንዳይደርስ ለማንቃት ተግተው እንደሚሰሩ አስታወቁ። በኖርዝ አሜሪካ ልጆችን ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥናቶችን ያካተተ መጽሐፍ የጻፉት ደራሲ ሐምራዊት ተስፋም ተጋባዥ መሆናቸው ታውቋል።
ወያኔ ህወሓት ያልከበደው ኢትዮጵያዊ ማነው?
ይኸነው አንተሁነኝ
ሌቱ መሽቶ ይነጋል፤ ሳምንታት ወራት ዓመታት በፍጥነት መንጎዳቸውን አላቋረጡም፤ ክረምትና በጋ ይፈራረቃሉ፤ ወቅቶችም ማንም ሳይረብሻቸው ጊዜያቸውን ጠብቀው እያለፉ ነው፤ አፍጣጭ ገላማጭ ያለባቸውም ማዘዣ ጣቢያቸው ከእኛ አይደለምና።
ዚምባብዌና ሶማሊያ በኢትዮጵያ
ይነጋል በላቸው
እስከ ዳግማይ ትንሣኤ ድረስ ብዙም ረፍዷል አይባልምና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች እንኳን ለ2005ዓ.ም የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ። ለቀጣዩ በዓልም ሁላችንንም በሰላም ያድርሰን።
በሆሳዕና "ማክበር" - በቀራንዮ "መስቀል"
ኤፍሬም እሸቴ
ታላቁ የክርስቲያኖች ጾም፣ ዐቢይ ጾም እነሆ የመጨረሻው "ሰሙነ ሕማማት"/ስቅለት ላይ ደረሰ። ለእምነቱ ተከታዮች የአጽዋማት ሁሉ በኩር እና ዋነኛ (ዐቢይ) እንደመሆኑ ከምንም በዓል በላይ በታላቅ መንፈሳዊ ስሜት የሚከበር ነው። የእምነቱ ተከታይ ላልሆነውም ወገን ቢሆን የሚኖረው ባህላዊ አንድምታ ከፍ ያለ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ታሪኩን በደረቅ ንባብ ለሚመለከተውም ቢሆን ከዕለት-ተዕለት ሕይወቱ ጋር ሊያስነጻጽረው የሚችለው ብዙ ቁም ነገር እንደሚያገኝበት ጥርጥር የለኝም።
ምርጫ የለም እንጂ ምርጫማ ቢኖር ...!
ፍቅር ለይኩን
የዛሬው ጽሑፌን በምርጫ ዙሪያ ካጋጠመኝ ትንሽ ቆየት ካለ ገጠመኜ ልጀምር። በደቡብ አፍሪካዊቷ ቢዝነስ ከተማ ጆሐንስበርግ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በትውልድ ደቡብ አፍሪካዊ የሆኑ ካህን፣ አባትና አገልጋይ የሆኑ በ60ዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ አንድ አዛውንት አባት አሉ።
የጎዳና ተዳዳሪው የወታደራዊ ደህንነትና መረጃ መኮንን ኮሎኔል ካሣሁን ትርፌ

ፍቅር ለይኩን
እንደ አለመታደል ሆኖ ከቅርብ የታሪካችን ዘመን እንኳን ብንነሳ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ የሆነ፣ ብሔራዊ ስሜት ያለው፣ ጠንካራ የሆነ ሕዝባዊ መሠረት ያለው የመከላከያ ኃይል ለመፍጠር እየተደረገ የነበረውና አሁንም እያየነው ያለው ሙከራ መንግሥት በተለዋወጠ ቁጥር ሂደቱ እየተገታ ከዚህ ደርሰናል።
አባይ ለሕዝብ ወይስ አባይ ለኢሕአዴግ?

ግርማ ካሳ
ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን ጨምሮ በርካታ የኢሕአዴግ ባለስልጣናት፣ በተለያዩ የአሜሪካና የአውሮፓ ከተሞች በመዘዋወር፣ ለአባይ ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ ሞክረዋል። ነገር ግን በበርካታ ከተሞች፣ ከዚህ በፊት ከነበረው በተለየ ሁኔታ፣ ጠንካራ ተቃውሞ የደረሰባቸው ሲሆን፣ አንዳንድ ከተሞችም፣ ተቃዋሚዎች ስብሰባውን ሙሉ ለሙሉ እስከመቆጣጠር የደረሱበት ሁኔታም እንደነበረም ታዝበናል።
"መሪ አጣን" እያሉ ማላዘን ይቁም!
መሪነት እና የመሪነት ወለፈንዲዎች
ታደሰ ብሩ
መግቢያ
ማኅበራዊ ለውጥንና እድገትን የሚመለከቱ ዓላማዎች በአንድ ወይም በጥቂት ሰዎች ጥረት የሚሳኩ አይደሉም። እነዚህ ትላልቅ ዓላማዎች እንዲሳኩ የብዙ ሰዎች የተባበረ ጥረት ያስፈልጋል። በርካታ ሰዎችን ለእንዲህ ዓይነቶቹ ግዙፍ ዓላማዎች ማነሳሳትና እና ማስተባበር ነው መሪነት (Leadership) የሚባለው።
ከፋውንዴሽኑ ጀርባ ...
ተመስገን ደሳለኝ
(ክፍል ፩)
ያለ ወቅቱ በደረሰ ዝናብ እየራሰች ያለችው አዲስ አበባ ዛሬም ከመለስ መንፈስ ተፅእኖ ነፃ አልወጣችም፤ ጣራና ግድግዳዎቿ እንዲህ በምስሉ እና በድርጅቱ አርማ መዥጎርጎሯን ያስተዋለ አንድ ቀልደኛ የባህር ማዶ ወዳጄ "እኔ ከሀገሬ ከወጣሁ በኋላ የኢህአዴግ ዋና ከተማ ሆነች እንዴ?" ብሎ ፈገግ አሰኝቶኛል። በእርግጥ ይህችን ቀልድ ስንፍቃት የምናገኘው ቁም ነገር፦ ከተማዋ በመለስ ውርስ ድንዛዜ ላይ መሆኗ፣ ...
"እያንዳንዱ ዜጋ ከራሱ ጋር ይነጋገር" አርቲስት ታማኝ በየነ
ታምሩ ገዳ
በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለው አስከፊ የሰብአዊ መብት ረገጣ ይቆም ዘንድ እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን አሰተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባው እና ከራሱ ጋር መነጋገር እንዳለበት ተገለጸ።
