ዱላ መመከት ያቃተው አማራ
- Details
- Hits: 12287
ይኸነው አንተሁነኝ
ህወሓት ሀገራችንን በገልበቱ መግዛት ከጀመረበት ግንቦት 1983 ዓ/ም ጀምሮ ለቁጥር የሚያታክቱ ለመስማት የሚያስጨንቁ ብዙ ቁም ስቅሎችን ፈጽሟል። የራሱን የህወሓትን ፓርላማ አንቀጽ 39ን በመመርኮዝ ራስን የመቻል ጥያቄ አቅርባችኋል ወይም ልታቀርቡ አስባችኋል በሚል ሰበብ ሰፊው የኦሮሞ ሕዝብ የስቃይ ዘመናትን አሳልፏል።
ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓባይ ወንዝ ዙሪያ ትልቅ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋል
- Details
- Hits: 4661
ፍቅር ለይኩን
በቅርቡ ሙስጠፋ አል ላባድ የተባለ ሊባኖሳዊ ፖለቲከኛና ጸሐፊ Egypt is Battling Ethiopia over the Nile Water በሚል ርዕስ አንድ መጽሐፍ አሳትሞ አውጥቷል። ይህን የአል ላባድን መጽሐፍ "አስ ሳፊር" የተባለ የሊባኖስ ዕለታዊውና ተነባቢ የዐረብኛ ጋዜጣ የመጽሐፉን አጭር ዳሰሳ በፊት ለፊት ገጹ ይዞ ወጥቶ ነበር።
የ"ኢሕአዴግ ደጋፊዎች" መልካም እንቅስቃሴ
- Details
- Hits: 4239
ግርማ ካሳ
በዳያስፖራ ቀንደኛ የኢሕአዴግ ደጋፊና የኢሕአዴግ ደጋፊዎች አስተባባሪ የሚባሉት፣ የሲቪሊቲ ፓልቶክ ክፍል ዋና አድሚን፣ አቶ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) ከአውራምባ ታይምሱ ዳዊት ከበደ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ አደመጥኩ። አባ መላ ጠንካራ ትችት በኢሕአዴግ ላይ ሰንዝረዋል። ይሄም ብዙዎችን ሳያስገርም አልቀረም። "አባ መላ፣ አራዳ ነው፤ ወያኔ ሊወድቅ ሲል ፍሬቻ አብሮቶ ታጠፈ" ያሉም አሉ። ፡) ፡) እኔ ግን ብዙ አላስገረመኝም።
ተገፊዎች የባህሪ ለውጥ አምጡ እንጂ!
- Details
- Hits: 2575
ገለታው ዘለቀ
ልትታተም ካሰበች አንዲት ልቦለድ ጽሁፍ ላይ አንድ የምናብ ሰው ከተገረመበት ነገር ተነስተን አጭር መልእክት ለማቀበል እንሞክራለን። ይህ የምናብ ሰው ወደ አንድ ሃገር ይሄድና በዚያ በአንድ ሆቴል ውስጥ ተቀምጦ ናሽናል ጂኦግራፊ የተሰኘውን የቴሌቪዥን ፕሮግራም ያያል። በወቅቱ ይተላለፍ የነበረው ፕሮግራም የዱር እንስሶች ኑሮ ነው።
በታዳጊ ወጣቶች ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ ችግሮችን ለማስወገድ የታሰበ መድረክ ተዘጋጀ
- Details
- Hits: 818
በ17 ዓመቷ ራሷን ያጠፋችው ወጣት ቤተሰቦች ልምድ ያካፍላሉ!
“በእኔ ቤተሰብ የደረሰ ልብ የሚሰብር ሀዘን በሌሎች ወገኖቼ ላይ ደርሶ ማየት አልፈልግም” (የኤደን ወላጅ አባት)
‘ልጄን እንደ ንግስት ነበር ያሳደኳት፤ የዚህ ሀገር ልጅ ምኑም አይታወቅም” የኤደን እናት ወ/ሮ በለጡ
ደራሲ ሐምራዊት ተስፋ በውይይቱ ላይ ትናገራለች!
የአማንዳ ቶድ ወላጅ እናት በውይይቱ ተካፋይ ናቸው!
Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 5ቀን 2005 ዓ.ም. May 13, 2012)፦ ባለፈው መስከረም 24 ቀን 2012 ዓ.ም በቫንኩቨር ካናዳ ህይወቷን ያጣችው የ17 ዓመት ታዳጊ ወጣት ኤደን ዘውዱ ቤተሰቦች በራሳቸው ቤተሰብ የደረሰ ሀዘን በሌሎች ወገኖች ላይ እንዳይደርስ ለማንቃት ተግተው እንደሚሰሩ አስታወቁ። በኖርዝ አሜሪካ ልጆችን ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥናቶችን ያካተተ መጽሐፍ የጻፉት ደራሲ ሐምራዊት ተስፋም ተጋባዥ መሆናቸው ታውቋል።
ወያኔ ህወሓት ያልከበደው ኢትዮጵያዊ ማነው?
- Details
- Hits: 1105
ይኸነው አንተሁነኝ
ሌቱ መሽቶ ይነጋል፤ ሳምንታት ወራት ዓመታት በፍጥነት መንጎዳቸውን አላቋረጡም፤ ክረምትና በጋ ይፈራረቃሉ፤ ወቅቶችም ማንም ሳይረብሻቸው ጊዜያቸውን ጠብቀው እያለፉ ነው፤ አፍጣጭ ገላማጭ ያለባቸውም ማዘዣ ጣቢያቸው ከእኛ አይደለምና።
ዚምባብዌና ሶማሊያ በኢትዮጵያ
- Details
- Hits: 866
ይነጋል በላቸው
እስከ ዳግማይ ትንሣኤ ድረስ ብዙም ረፍዷል አይባልምና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች እንኳን ለ2005ዓ.ም የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ። ለቀጣዩ በዓልም ሁላችንንም በሰላም ያድርሰን።
በሆሳዕና "ማክበር" - በቀራንዮ "መስቀል"
- Details
- Hits: 677
ኤፍሬም እሸቴ
ታላቁ የክርስቲያኖች ጾም፣ ዐቢይ ጾም እነሆ የመጨረሻው "ሰሙነ ሕማማት"/ስቅለት ላይ ደረሰ። ለእምነቱ ተከታዮች የአጽዋማት ሁሉ በኩር እና ዋነኛ (ዐቢይ) እንደመሆኑ ከምንም በዓል በላይ በታላቅ መንፈሳዊ ስሜት የሚከበር ነው። የእምነቱ ተከታይ ላልሆነውም ወገን ቢሆን የሚኖረው ባህላዊ አንድምታ ከፍ ያለ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ታሪኩን በደረቅ ንባብ ለሚመለከተውም ቢሆን ከዕለት-ተዕለት ሕይወቱ ጋር ሊያስነጻጽረው የሚችለው ብዙ ቁም ነገር እንደሚያገኝበት ጥርጥር የለኝም።
ምርጫ የለም እንጂ ምርጫማ ቢኖር ...!
- Details
- Hits: 888
ፍቅር ለይኩን
የዛሬው ጽሑፌን በምርጫ ዙሪያ ካጋጠመኝ ትንሽ ቆየት ካለ ገጠመኜ ልጀምር። በደቡብ አፍሪካዊቷ ቢዝነስ ከተማ ጆሐንስበርግ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በትውልድ ደቡብ አፍሪካዊ የሆኑ ካህን፣ አባትና አገልጋይ የሆኑ በ60ዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ አንድ አዛውንት አባት አሉ።
የጎዳና ተዳዳሪው የወታደራዊ ደህንነትና መረጃ መኮንን ኮሎኔል ካሣሁን ትርፌ
- Details
- Hits: 11178

ፍቅር ለይኩን
እንደ አለመታደል ሆኖ ከቅርብ የታሪካችን ዘመን እንኳን ብንነሳ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ የሆነ፣ ብሔራዊ ስሜት ያለው፣ ጠንካራ የሆነ ሕዝባዊ መሠረት ያለው የመከላከያ ኃይል ለመፍጠር እየተደረገ የነበረውና አሁንም እያየነው ያለው ሙከራ መንግሥት በተለዋወጠ ቁጥር ሂደቱ እየተገታ ከዚህ ደርሰናል።


