ዋና ገጽ ዋና ገጽ
 

ግልጽ ደብዳቤ (ፀሐይ አሳታሚና ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ) – (ሊያነቡት የሚገባ) Print E-mail

ክፍሌ ሙላት (የኢነጋማ ፕሬዝዳንት) - በግል

ሲሞላልኝ በሳምንት ካልሆነልኝ ደግሞ በአስራ አምስቱ ሰላምታዬን ካሉበት የማደርሳቸው ወዳጆች አሉኝ።  ለአገር ምድሩ ሳይሆን በጣት የሚቆጠሩ። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሙያ ባልደረባዬ ኤልያስ ወንድሙ ነው። ትውውቃችን የመንገድ ላይ አይደለም። የኔዎቹ የነፃ ፕሬስ አባላትና የሃገሬ ሰላም ወዳድ ኃይሎች በግፈኞቹ የሕወሃት አባላትና ሹመኞች የሚሰደዱበት የሚታሰሩበት ብሎም የግፍ ፅዋ የሚቃመሱበት በእነዚያ የትግል፣ የፈተናና የፍልምያ ዓመታት የልብ ወዳጅና ለእውነት የቆሙ በመብራት በሚፈለጉበት የወያኔ የግፍ ዘመናት። ዛሬም ይህ ሐቅ ገሃድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የተስፋው ቃል፣ የአህአዴግ ቃል Print E-mail

ተመስገን ደሳለኝ

ተስፋ ቆርጬ አላውቅም። ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር ሳያጋጥመኝ ቀርቶ አይደለም። ብዙ ጊዜ ገጥሞኝ ያውቃል። ነገር ግን የብዙ ሀገራት ተሞክሮን ካየክ ተስፋ እንድትቆርጥ አይገፋፋህም። ለምን? ካልከኝ ብዙዎች ‹‹ሞቱ፣ ተቀበሩ›› ሲባሉ እንደ ገና መግነዛቸውን በጥሰው ሲያቸንፉ ታያለህና። በሀገራችንም ቢሆን ‹‹አለቁ፣ ደቀቁ›› የተባለላቸው ሟርቱን አቸንፈው አይተሀል። ‹‹እፍኝ የማይሞሉ…›› ሲባል የነበረበትንም ዘመን መቼም ትረሳዋለህ ብዬ አላስብም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ይድረስ ለአነስተኛ እና ጥቃቅን ስድብ አምራቾች! Print E-mail

አቤ ቶኪቻው

በመጀመሪያም

ይህ ፅሁፍ ባለፈው አርብ ለወጣችው ለምናፍቃት ፍትህ ጋዜጣ ልኬው ታትሞም የነበረ ነው። ታድያ ለፍትህ ስፅፈው በተቻለኝ አቅም በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ያሉት ፈላጭ ቆራጮቻችን ደም ብዛታቸው ከፍ እንዳይል በመጨነቅ አንዳንድ ሃሳቦች ላይ ቁጥብ ስድር ለማለት ሙከራ አድርጊያለሁ። ምክንያቱም ሰዎቹ ደማቸው ሲፈላ የሚያደርጉትን አያውቁትምና፤ የአዲሳባ ወዳጆቼ እንዲሁ ያለባቸው ጦስ ሳያንሳቸው እኔ ደግሞ ተጨማሪ አልሆንባቸውም ብዬ ነው። እናም ይህ ፅሑፍ ዛሬ ለዌብ ሳይቶች ስልከው ትንሽ ከለስ ከለስ አድርጌዋለሁ…

እስቲ አንብቡልኝ…!

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የአሳዛኙ ዜና ኀዘን Print E-mail

ወለላዬ ከስዊድን This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

መቼም ተስፋዬ ገብረአብ ከጻፈ አንድ ትዝታ የሚጭር ወይም ስሜት የሚነካ ነገር አያጣም። ባለፈው ሣምንት ”አሳዛኝ ዜና” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፉ ደግሞ ስሜቴን መንካት ሳይሆን በክፉ የኀዘን ትዝታ ውስጥ ዘፍቆኝ ሰነበትኩ። እንዴት ሆኖ ማለትዎ አይቀርም፤ እነሆ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ግቡን የሳተ ቀስት! Print E-mail

‘ኢሕአፓ’ - አዲሱ የነጻ ፕሬስ ጠላት!?

ከአትክልት እና ጓደኞቹ

የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ላለፉት 20 ዓመታት በእሳት የተፈተኑ ቁርጠኞች ናቸው። እስርና እንግልቱን በተደጋጋሚ የወጡበት የወረዱበት ሸክም ነው።  በጠራራ ፀሀይ በወያኔ ጥይት የተገደሉትን መርሳት ይከብዳል። ህክምና ተነፍገው ዘብጥያ ውስጥ የሞቱትንም ማስታወስ እንዲሁ... ይሰቀጥጣል። ዛሬም ወፍራም ወፍራም ክስ ተለጥፎባቸው ቃሊቲ ውስጥ የሚጉላሉትንም ልብ ይሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በሱማሊያ የኢትዮጵያ ጦር ሰፈር በአጥፍቶ ጠፊዎች ተጠቃ! Print E-mail

አልሸባብ 10 ወታደሮች ገደልኩ ብሏል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2004 ዓ.ም. January 25, 2012)፦ በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ጠቅላይ ሰፈር ላይ የአልሸባብ አጥፍቶ ጠፊ በሚኒባስ ሙሉ የታጨቁ ቦምቦች ማፈንዳቱ ተዘገበ። በጥቃቱ 10 የኢትዮጵያ ወታደሮች መግደሉን አልሸባብ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አፈር ስሆን፤ ፌስ ቡክዎ ላይ አድ ያድርጉኝ! Print E-mail

አቤ ቶኪቻው

ውድ ጠቅላይ ሚኒስትር… ብዬ ልጀምር ነበር “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት!” ሲሉኝ ታየኝና ተውኩት።

ቆይ እስቲ ወዳጄ መጀመሪያ ከእርስዎ ጋር ሰላምታ እንለዋወጥ። እርስዎ ኖት ቀሪ ሃብቴ…! እንዴት አሉልኝ…? ጤናዎ አማን ነው? ግራ ቀኙ ሁሉ ሰላም ውሎ አድሯል? ጎሽ እንዲህ ነው እንጂ የጨዋ መልስ! እርሱ ጠባቂው ለወደፊቱም እቅፍ ድግፍ አድርጎ ይጠብቅልኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ምርኮኛ - ቅኝት መስፍን ማሞ ተሰማ (ሊያነቡት የሚገባ) Print E-mail

የመጸሐፉ ደራሲ ቆንጅት ብርሃን

መንደርደሪያ

ደምና ዕንባ ተቀላቅሎ በብዕር ሲቀሰም ምንን ይወልዳል? ምርኮኛ! ምርኮኛ የደም መፅሀፍ ነው።  የዕንባ መፅሀፍ። የአንድ ትውልድ ደም፤ የአንድ ትውልድ ዕንባ የተተረከበት የደም ዕንባ ታሪክ። ምርኮኛ አንባቢን ምርኮኛው አድርጎ በትርክቱ ባህር እየደፈቀ፤ ትንፋሽ እስኪያጥር ነፍስ እስክትቃትት አካልና መንፈስን ረግጦ የሚገዛ፤ ሃያል የደም ዕንባ ታሪክ ነው - ያልታደለው ትውልድ ታሪክ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በአፋር ክልል ለታገቱት ጀርመናዊያን አርዱፍ ኃላፊነት ወሰደ Print E-mail

‘5ቱ ጎብኝዎች የሞቱት በኢትዮጵያ መንግስት ጥይት ነው’ አርዱፍ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 14 ቀን 2004 ዓ.ም. January 23, 2011)፦ ባለፈው ሳምንት ለ5 ጎብኝዎች ሞት ምክንያት ለሆነው እና ለ27 ጎብኝዎች ላይ ለተቃጣው ጥቃት በህወሀት መራሹ የኢትዮጵያ ወታደሮችና በአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (አርዱፍ) መሀከል በተነሳ ጦርነት መሆኑንና ታጋቾቹ ሁለት ጀርመናዊያን በእጁ እንደሚገኙ አርዱፍ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ፖለቲካን መጋፈጥ እንጂ ማምለጥ አያዋጣም Print E-mail

ሉሉ ከበደ

የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነው። አንድ ቀን አባቱን ጠየቀው፤ ” አባባ ፖለቲካ ምንድነው?” “ ጥሩ ጥያቄ ነው ልጄ! ቁጭ በል በምሳሌ አስረዳሀለሁ። “ ይልና አባት ልጁን ካስቀመጠ በሗላ ‘’ፖለቲካ ማለት እንግዲህ ይህን ቤታችንን እንደ ሀገር ቁጠረው። ቤታችን ሀገር ማለት ነው። በቤታችን ውስጥ ስራ እየሰራሁ ገንዘብ የማመጣ እኔ ነኝ።  እኔን እንደ ካፒታሊዝም ቁጠረኝ። እኔ ካፒታሊዝም እባላለሁ። እናትህ ደግሞ እኔ በማመጣው ገንዘብ ለቤታችን የሚያስፈልገንን ሁሉ ምግብም ልብስም ሌላውንም እየገዛች ታስተዳድረናለች ማለት ነው። እናትህን ደግሞ እንደመንግስት ቁጠራት። እናትህ መንግስት ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 126

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!

Banner