Home ዋና ገጽ
ለሎሬት ፀጋዬ ገ/መድኅን መታሰቢያ አዲስ ድረ ገጽ ተከፈተ PDF Print E-mail
Thursday, 24 July 2008 13:49

L. Tsegaye G/MedhinEthiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ለታዋቂው ኢትዮጵያዊ የሥነ ጥበብ አባት ለሎሬት ፀጋዬ ገብረመድኅን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በመጀመሪያ ስሙ መጠሪያ ”ፀጋዬ” የተሰኘ ድረ ገጽ መከፈቱንና በይፋ ሥራውን መጀመሩን ድረ ገጹ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው ኢ-ሜይል ገለጸ።

Read more...
 
አንድነት ምርጫ ቦርድ የጠየቀውን ማሻሻያዎች አሟልቶ አስገባ PDF Print E-mail
Thursday, 24 July 2008 13:31

ስሙን በሚመለከት ማሻሻያ ሳያደርግ ቦርዱ እንዲወስንለት ጠየቀ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ”አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ” ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ ፈቃድ መጠየቂያ ማመልከቻ ካስገባ በኋላ፤ ባለፈው ሣምንት ኀሙስ ዕለት ምርጫ ቦርድ በጽ/ቤቱ በኩል አስር ነጥቦችን ዘርዝሮ ማሻሻያዎችና ለውጦች እንዲደረግባቸው ለፓርቲው በደብዳቤ አሳውቆ በነበረው መሠረት፣ ፓርቲው በዛሬው ዕለት በደብዳቤ ምላሽ መስጠቱን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

Read more...
 
የቴዲ አፍሮን ፎቶ በፊት ገጹ ያተመው ጋዜጣ ተከሰሰ PDF Print E-mail
Wednesday, 23 July 2008 17:16

Teddy AfroEthiopia Zare (ኀሙስ ሐምሌ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. July 24, 2008)፦ ቴዲ አፍሮን ፖሊሶች ሲጎትቱት የሚያሳየውን ፎቶግራፍ (በግራ በኩል የሚታየውን ፎቶ) በፊት ገጹ ላይ ያወጣው በሀገር ውስጥ የሚታተመው ”መሰናዘሪያ” የተባለው ጋዜጣ በፎቶግራፉ ምክንያት መከሰሱን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው መረጃ አስረዳ። የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ወሰንሰገድ መሸሻን ፖሊስ ጠርቶታል።

Read more...
 
እነኢ/ር ኃይሉ ”ቅንጅት”ን በፍ/ቤት ተከለከሉ PDF Print E-mail
Wednesday, 23 July 2008 12:04

Eng. Hailu Shawelበመኢአድ ስም ሊቀጥሉ ይችላሉ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የቅንጅት አመራሮች ከእስር ከተፈቱ በኋላ በተፈጠረው ልዩነት ኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመሩት ቡድን ”ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ” ይገባኛል በማለት ምርጫ ቦርድን ከስሶ ሲከራከር የነበረ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት የዋለው ችሎት ለምርጫ ቦርድ ወስኖ እነኢ/ር ኃይሉ ሻውልን ”ቅንጅት” የሚለውን ስም መከልከሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው መረጃ ጠቆመ። 

Read more...
 
በቅንጅት ስም የተሰበሰበው ገንዘብ የማነው? PDF Print E-mail
Wednesday, 23 July 2008 11:10

ድጋፍ አሰባሳቢዎቹ መልስ አላቸው

በኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመራው ቡድን ቅዳሜ ሰኔ 13 ቀን እና እሁድ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔ አድርጎ አመራሮቹን መምረጡ አይዘነጋም። በጠቅላላው ጉባዔ ም/ፕሬዝዳንትና የሰሜን ኢትዮጵያ ቀጠና ኃላፊ ሆነው የተመረጡት አቶ አባይነህ ብርሃኑ፤ የጉባዔው መዝጊያ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠታቸውን መዘገባችን አይዘነጋም።

Read more...
 
“ዶ/ር ብርሃኑ ያቋቋመውን ንቅናቄ አልተቀላቀልኩም። የሚወራው ሁሉ ሐሰት ነው” ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ PDF Print E-mail
Wednesday, 23 July 2008 03:42

የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ የቀድሞ ም/ሊቀመንበርና፤ ቅንጅት አዲስ አበባን ተረክቦ ቢሆን ኖሮ ለአዲስ አበባ በምክትል ከንቲባነት ተመርጦ የነበረው ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ በተለይ በሀገር ውስጥ ባሉ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኀን ግንቦት 7 ንቅናቄን እንደተቀላቀለ ተደርጎ የሚናፈሰውን ወሬ አስመልክቶ በሀገር ውስጥ የሚታተመው የእንቢልታ ጋዜጣ ቃለምልልስ አድርጎለታል።

Read more...
 
ትናንት የቴዲ አፍሮን ችሎት ከተከታተሉት አስሩ ታስረው፣ 5ቱ ዛሬ ፍ/ቤት ቀረቡ PDF Print E-mail
Tuesday, 22 July 2008 12:15

Teddy Afroየታሰሩት “ችሎት ረብሻችኋል፣ ድንጋይ ወርውራችኋል” በሚል ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ በትናትናው ዕለት የቴዲ አፍሮን ችሎት ለመከታተል ከመጡ ችሎት ተከታታዮች መካከል አስሩ ታሰሩ። በዛሬው ዕለትም ፖሊስ ሜክሲኮ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ነክ ፍርድ ቤት አምስቱን አቅርቧቸው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀባቸው ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ፈቅዶለታል። 

Read more...
 
"ኢትዮጵያውያን በሱዳን ግድያና ድብደባ ደረሰባቸው" ኢ.ሱ.ድ.ጉ.ኮ. PDF Print E-mail
Tuesday, 22 July 2008 08:34

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ (ኢ.ሱ.ድ.ጉ.ኮ.) "ኢትዮጵያውያን በሱዳን ግድያና ድብደባ ደረሰባቸው (ሌላው ዳርፉር)" በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ በሱዳን ሀገር ለብዙ ዓመታት በስደት በሚኖሩና ቋሚ የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቃት እየተሰነዘረባቸው መሆኑን አስታወቀ።

Read more...
 
በቤጂንጉ ኦሎምፒክ ተሳታፊ አትሌቶች ስም ዝርዝር ታወቀ PDF Print E-mail
Tuesday, 22 July 2008 03:57

የእነ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ሥራ አስኪያጅ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የፊታችን ነሐሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. (August 8, 2008) በሚከፈተው የቤጂንጉ ኦሎምፒክ የሚሳተፉ አትዮጵያውያን አትሌቶች ታወቁ። በዚህ በቻይና በሚደረገውና 17 ቀናት በቀሩት ኦሎምፒክ ላይ ኢትዮጵያ በአምስት የተለያዩ ውድድሮች በሴቶችም በወንዶችም ትሳተፋለች።

Read more...
 
ቴዲ ለሚቀጥሉት 75 ቀናት ቃሊቲ ይቆያል PDF Print E-mail
Monday, 21 July 2008 06:29

Teddy Afro- ክሱን ተከላከል ተባለ

- ወዳጅ ዘመዶቹ በእንባ ተራጭተዋል

Ethiopia Zare (ሰኞ ሐምሌ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. July 21, 2008)፦ አዲስ አበባ በፍተኛ ዝናብ ተውጣለች። ዝናቡን ከምንም ያልቆጠሩ የቴዲ አፍሮ ቤተሰቦች፣ ጓደኞችና አድናቂዎቹ በከፍተኛው ፍርድ ቤት መግቢያ በር ላይ በተለመደው ሁኔታ ሰልፍ ይዘዋል። ከላይ ስለሚወርድባቸው ዝናብ አንድም ያዘነ ፖሊስ አለነበረም። “ምናለበት ውስጥ ገብተን ብንጠብቅ?” የሚለው ጥያቄም መልስ አላገኘም። በተለመደው ሰዓት ከጠዋቱ 2፡45 ሲሆን፣ ወደ ግቢው እንድንገባ ተፈቀደ።

Read more...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 24
 

አዲስ ግጥም

ኢትዮጵያዬ (ከትንሣዔ)  

ያንተ ሽበት (ከትንሣዔ) 

አውቀን አንድ እንሁን (ከትንሣዔ)  

የኔ ሽበት (ከወለላዬ)

ወደቀሪዎቹ ግጥሞች ውሰደኝ ...