|
ዳንኤል አበራ (
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
) ኢትዮጵያ ከዘመነ መሣፍንት ተላቅቃ አንፃራዊም ቢሆን ወደ ተረጋጋ ማዕከላዊ አስተዳደር የተሸጋገረችበት ዘመን። አባ ዳኘውም እምዬም እየተባሉ ሲጠሩ የነበሩት አፄ ምኒልክ ሥልጣን ያደራጁበት እና ኢትዮጵያን ያሰሱ አውሮፓውያንን ባላሰለሰ የመሣሪያ ስጦታም ግዢም ጥያቄ የወተወቱበት ዘመን፤ ኋላም ተክለፃዲቅ መኩሪያ እንደጻፉልን “ባመጣው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ ተፈጠመ ጣሊያን አበሻ እንዳይደርስ” ከተባለበት የጣሊያን መንግሥት ጭምር የመሣሪያ ስጦታ ተረክበው ምኒልክ ጦራቸውን ያደራጁበት ዘመን፤ አውሮፓውያን አህጉራትን እንደቅርጫ ሥጋ የተከፋፈሉበት ዘመን። አፍሪካም፣ ኢትዮጵያም የዚህ ዕጣ ፈንታ ተቋዳሽ እንዲሆኑ በዝግ ተወስኖ ለአፄ ምኒልክና መንግሥታቸው መልዕክት የተነገረበት ዘመን፤ አፄ ምኒልክም መልዕክቱን ሰምተው እግዜር ይስጥልኝ ውሳኔያችሁን አልቀበልም ያሉበት፣ የጦርነትም ስጋት ያንዣበበት ዘመን ነበር ዘመኑ። |
|
ሙሉውን አስነብበኝ ...
|