|
Interview -
Interview
|
|
”ግዕዝ ብማር ደስ ይለኛል”
ወጣቱ፣ እውቁና ታዋቂው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከእስር ከተለቀቀ ሦስት ወር የሆነው ሲሆን፣ በውጭ ሀገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን የመገናኛ ብዙኀን ጋር ሰፋ ያለ ቃለምልልስ ያደረገው ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ ጋር ሲሆን፤ ቃለምልልሱን ያደረገው ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ያሬድ ክንፈ ጋር ነው። በዚህ ቃለምልልስ ላይ ያሬድ በቴዲ አፍሮ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ፣ በቴዲ እስር ቤት ቆይታ ላይ፣ በድምፃዊው የሙዚቃ፣ የግጥምና የመድረክ ሥራ ላይ፣ በአርቲስቱ የግል ሕይወት ጉዳይ ላይ፣ ባለፈው ጥቅምት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም ለምን ”ያስተሰርያል” የሚለውን ዘፈን እንዳልዘፈነ፣ በስዊድንና በኖርዌይ ኮንሰርቶቹ እሰጥ አገባና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጥያቄዎችን ለአርቲስት ቴዲ አፍሮ አቀርቦለታል። አርቲስት ቴዲ አፍሮን ለቃለምልልሱ እያመሰገንን፤ መልካም ንባብ ለአንባቢዎቻችን እንመኛለን! |
|
ሙሉውን አስነብበኝ ...
|
|
Art -
አስተያየትArt Opinion
|
|
ዘነበ በቀለ ርዕሱ ብዙዎችን ያሳስታል ብዬ አልገምትም። የሁለቱንም ዘፋኞች ሙዚቃ አገናዝቦ መረዳት የሚቻል ነውና። አሪታ በልጅነት ዘመኗ ”ሬሰኩዩሚ” እያለች ያቀነቀነችው ሙዚቃ በአንድ በኩል የሙዚቃው ርዕስ ጭንቀቷን ገላጭ ቢመስልም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የድምፅዋን ልክ ያሳየችበት ዕፁብ ድንቅ የሆነ ዜማዋ ነው። ኢትዮጵያዊቷ አሪታ ፍራንከሊን ደግሞ በባህላዊ መንገድ ችግርን አምቆ መያዝ እንጂ ለአደባባይ አስጥቶ ማሳየት የተለመደ አይደለምና ሁሉን ቻይ ሆና መከራዋን የምትገፋው ድምፃዊቷ ማሪቱ ለገሠ ነች። |
|
ሙሉውን አስነብበኝ ...
|