Home
ግንቦት 7 ንቅናቄ በስዊድን Print E-mail
User Rating: / 17
PoorBest 
Articles
Saturday, 28 June 2008 07:13

ህዝባዊ ውይይቱ ምን ይመስል ነበር?

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን

ሠላምና ጤናውን ከነቤተሰብህ ያበዛልህ ዘንድ የዘወትር ምኞቴ ነው። ለእመቤትህና ለልጃችሁ የከበረ ሠላምታዬን አቅርብልኝ። ዛሬ የማወጋህ “ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ” የተሰኘውና በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አዲስ ንቅናቄ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከተማ ከህዝብ ጋር ያደረገውን ውይይት ነው። ውይይቱ ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ስላወቅሁ ከስቶክሆልም 220 ኪሎ ሜትር ርቄ ከምኖርበት ሳንድቪከን ከተማ ወደዚያው አመራሁ። ንቅናቄውን በመወከል ዶ/ር ብርሃኑ እና አቶ ቸኮል ጌታሁን ነበር የተገኙት። አቶ ቸኮል የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባል የነበረ ሲሆን፣ አሁን በስዊድን ስደተኛ ነው።

Read more...
 
"ኢትዮጵያውያን በሱዳን ግድያና ድብደባ ደረሰባቸው" ኢ.ሱ.ድ.ጉ.ኮ. Print E-mail
User Rating: / 2
PoorBest 
ኢትዮ-ሱዳን ድንበር
Tuesday, 22 July 2008 08:34

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. July 22, 2008)፦ የኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ (ኢ.ሱ.ድ.ጉ.ኮ.) "ኢትዮጵያውያን በሱዳን ግድያና ድብደባ ደረሰባቸው (ሌላው ዳርፉር)" በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ በሱዳን ሀገር ለብዙ ዓመታት በስደት በሚኖሩና ቋሚ የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቃት እየተሰነዘረባቸው መሆኑን አስታወቀ።

Read more...
 
ከወርቅ የበለጠ ሜዳሊያ (ከግርማ ካሣ) Print E-mail
User Rating: / 9
PoorBest 
Articles
Sunday, 24 August 2008 16:23

ግርማ ካሣ - ቺካጎ ( This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it ) እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም.

Tirunesh Dibaba, Beijing Olympic, 20080822Kenenisa Bekele, Beijing Olympic, 20080823

“ድሮ መች ነበረ ዘር መርጦ ጎሮቤት

በጠዋቱ በጥንቱ በነአባብዬ ቤት

እድር መቃብሩ ሲያሰባስባቸው

መች ይጠየቅ ነበር የዘር ሃረጋቸው” 1

በቤጂንግ አትሌቶቻችን በወርቅ፣ በብር እና በነኀስ የተሰሩ ሜዳሊያዎች ብቻ አልነበረም ያስገኙት። የኦሎምፒክ ኮሚቴ ከሚሰጠው ሜዳሊያዎች ያለፈ፣ የኦሎምፒክ ባለሥልጣናት የማያወቁት፣ እጅግ በጣም የከበረ የሜዳሊያዎች ሁሉ ሜዳሊያ ይዘውልን መጥተዋል። … አሲዮ ቤሌማ!!!

Read more...
 
ለሱዳን ተቆርሶ የተሰጠውን መሬት አስመልክቶ በኢትዮጵያ ኤምባሲ የተቃውሞ ሠልፍ ተካሄደ Print E-mail
User Rating: / 5
PoorBest 
ኢትዮ-ሱዳን ድንበር
Friday, 01 August 2008 06:05

Ethiopia Zare (ዓርብ ሐምሌ 25 ቀን 2000 ዓ.ም. August 01, 2008)፦ በስዊድን የሚገኙና ለእግር ኳስ ውድድር በስቶክሆልም ለመሳተፍ ከተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት የመጡ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የተቃውሞ ሠልፍ በትናንትናው ዕለት በኢትዮጵያ ኤምባሲ ተካሄደ። የተቃውሞ ሠልፉ ዓላማ የኢህአዴግ መንግሥት ከምዕራብ ኢትዮጵያ ቆርሶ ለሱዳን መንግሥት የሰጠውን መሬት በመቃወም ነው።

Read more...
 
በአ.አ. የመሬት አስተዳደር ኃላፊዎች ከ3.7 ሚሊዮን ብር በላይ በማካበታቸው ታሰሩ Print E-mail
News
Monday, 25 August 2008 13:10

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ሊዝ ጽ/ቤት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ትንሣዔ ደነቀ፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር መምሪያ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ዳንኤል ስዩም እና በቦሌ ክፍለ ከተማ መሐንዲስ የሆኑት ወ/ሮ ማኅሌት አምሳሉ ከሕጋዊ ገቢያቸው ውጭ ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ በግል የባንክ አካውንታቸው ውስጥ ተገኝቷል በሚል ታሰሩ።

Read more...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 59