መጻሕፍት

የክሽፈት እንጉርጉሮ፣ ታሪክ ላይ ተሸንቅሮ!

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክካሣሁን ዓለሙ

"አንድ ሰው በአደባባይ ሲናገርም ሆነ ጽሑፍ አሳትሞ ሲያሰራጭ ራሱን አጋልጦአል፤ የተናገረው ወይም የጻፈው መቶ በመቶ ያህል በራሱ ጉዳይ ላይ ብቻ ከሆነ፣ የመተቸት ወይም ሐሳብ የመስጠት ግደታ የለብንም፤ ነገር ግን የተናገረው ወይም የጻፈው በአገርና በሕዝብ ጉዳይ ላይ ከሆነ፣ የዚያ አገር ዜጋ ሁሉ በጉዳዩ ውስጥ የመሳተፍና ሐሳቡን በሙሉ ነጻነት የመስጠት መብት አለው።"

(ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም፣ መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ፣ ገጽ78-79)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር ጋሻው ስንኞች ከባህር ማዶ

Dr. Gashawዓለማየሁ ታዬ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

በያዝነው ዓመት የአማርኛ ቋንቋን የሥነ ግጥም እልፍኝ ካደመቋት አዳዲስ መድበሎች መካከል “ስንኞች ከባህር ማዶ” እጄ ገብታለች። በአንድ መቶ ሦስት ገጾች ተደጉሳ የሕትመት ብርሃን የሞቀችው ይህች መድበል 72 የአማርኛ እና ስምንት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ግጥሞችን ይዛለች። ገጣሚው በመግቢያው እንዳብራራው ግጥሞቹ የተጻፉት ባለፉት 38 ዓመታት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ በፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም“ነፍስ ካለ፣ መፍጨርጨር አይቀርም!”

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በሐምሌ 1955ዓ.ም የወጣው መነን መጽሔት፣ (7ኛ ዓመት፣ ቁ.10 ዕትም፣ በገጽ 27) ላይ እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቶ ነበር፤ “እኚህ የ33 ዓመት ወጣት በአባታቸው ጎንደሬ፣ በእናታቸውም ይፋቴ ሲሆኑ፣ በአማርኛ የበሰሉ በመሆናቸው የመናገርና የማስረዳት ስጦታ ያላቸው ትሁት ወጣት ናቸው፤” ሲል ይገለጻቸዋል። ለጥቆም የወጣቱን መስፍን ወልደ ማርያም ሦስት ሐሳቦች እንደሚከተለው አስፍሮት ይገኛል። “ማናችንም በዘመኑ የምንገኝ ትውልዶች በምናውቀውና በተማርነው ችሎታችን ተሽለን ተገኝተን፣ የዚህ ዕድል ተሣታፊ ለመሆን የሚጓጉ ወንድሞቻችንን ለመርዳት የምንቦዝንበት ትርፍ ጊዜ እንዲኖረን አያሻም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የላትቪያው (ልብወለድ መጽሐፍ) በገበያ ላይ ዋለ

የላትቪያው - በግርማ ደገፋ ገዳ Yelativiaw by Girma Degefa Gedaደራሲ፡ ግርማ ደገፋ ገዳ

ገጽ፡ 496

ዋጋ፡ 20 ዶላር

“የላትቪያው” በፍቅር፣ በፖለቲካ፣ በሰብአዊ መብቶችና በሀገራዊ እውነታዎች ዙሪያ የሚያውጠነጥን፤ 496 ገጾች ያሉት፣ ስፋትና ቁመቱ አነስ ተደርጎ ለየት ባለ ሁኔታ የታተመ ልብወለድ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ፤ የተለያየ አመለካከት ያላቸውን ግለሰቦች እይታ በጉልህ የሚያሳይ ከመሆኑ ባሻገር፤ አንባቢያንን እያስገረመ፣ እያሳዘነና እያስደሰተ ከገጽ ወደ ገጽ ይዞ የሚሄድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሥነ-ምግባር መሠረት - “ብፁዓን ንጹሓነ ልብ”

ብፁዓን ንጹሓነ ልብ - እጓለ ገብረዮሐንስ (ዶ/ር)ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

ያ ሰው ሞተ አሉኝ፣ እንዴት ያ ሰው ይሙት?

በሕይወት ሲያስተምር፣ ለሰው ልጆች ሕይወት፣

ተቀበረ አሉኝ፣ ከቶ እንዴት ይቀበር፣

ሙት ሕያው እንዲሆን፣ በቁሙ ሲያስተምር!

(“ስለ ክርስቲያን ሥነ-ምግባር መሠረት” (ብፁዓን ንጹሓነ ልብ)፤ ገጽ 165)

ከወራት በፊት “የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” (ዘየአውዱት ከመ ዳመና)”ን ባወጣሁ ጊዜ እንደገለጽኩት፣ “የዶ/ር እጓለ ባለቤት ከባሕር ማዶ መጥተው፣ “የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” የተባለውን መጽሐፍ በድጋሚ በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት እያሳተሙት መሆኑንና በቅርቡ እንደሚወጣም ጓደኛቸው ዶ/ር ምክረሥላሴ አበሰሩኝ ስል ጽፌ ነበር። በተጨማሪም፣ ደራሲው የአባታቸውን፣ የአለቃ ገብረ ዮሐንስ ተሰማንም ታሪክና ስራዎች የሚዘክር መጽሐፍም አዘጋጅተው ስላለፉ፣ እርሱም ጭምር ከላይ በተጠቀሰው ማተሚያ ቤት እየታተመ እንዳለና መገባደጃውም ላይ እንደሆነ” ዶ/ር ምክረሥላሴን በመጥቀስ ጽፌ እንደነበረ የሚታወስ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመቀሌ ጥንታዊ ቀልዶች (ተስፋዬ ገብረአብ)

ተስፋዬ ገብረአብ (“እፍታ - ቅፅ አንድ” (1991) መጽሐፍ)

በመቀሌ ከተማ የቀልድ ነገር ሲነሳ፣ ካሳ ደበስ እና አስፋቸው ፈቃዱም አብረው ይነሳሉ። በእነዚያ የሩቅ ዘመናት ከማለዳው አራት ሰአት ጀምሮ የጠላ ገበያ ይደራባት በነበረችው መቀሌ ቀልድ ትልቅ ስፍራ ይሰተው ነበር። ጥርስ የማያስከድኑ ቀልዶችም በጠላና በአረቄ ቤቶች ይንቆረቆራሉ። ሁለቱ የቀልድ አባቶች ዛሬ በህይወት ባይኖሩም፣ ከተማይቱ ነዋሪዎች ግን ዛሬም ድረስ በፈገግታ ያነሳሱዋቸዋል። በአማርኛ ሲቀርቡ ያስቁ ይሆን?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

Template by A4