ዋና ገጽ መጣጥፍ አስተያየት ሃምሳ አለቃ ደሳለኝ (ቴድሮስ ኃይለ)
 
ሃምሳ አለቃ ደሳለኝ (ቴድሮስ ኃይለ) Print E-mail
User Rating: / 0
PoorBest 

ቴድሮስ ኃይለ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

ከደርጉ የገበሬ ማኅበር ካድሬዎች በገራገርነቱ የሚታወቀው የጎጃሙ ቆምጫምባው እንደዋዛ አለ ተብሎ ከሚነገርለት አባባል አንዱ፤ ጋዜጠኛ ”ለመሆኑ ክቡርነትዎ የአሜሪካንን ኢምፔሪያሊዝም እንዴት ይመለከቱታል?” ሲል ለጠየቃቸው፤ ጓድነታቸው ባልተንዛዛ አማርኛ ”የጎሪጥ ነው የማየው” ሲሉ ቆፍጠን ያለ መልስ እንደሰጡ በቀልድ መልክ ሲነገርና፤ ለአንዳንድ ግልገል ካድሬዎችና አድርባዮችም ጭፍን አቋምና ባዶ ፕሮፓጋንዳ እንደ ምሳሌ ሲቀርብ ይስተዋላል።

 

ከጭፍን ካድሬዎችና ከእበላ ባይ ጭፍሮች ያልተላቀቀው የሀገራችን ፖለቲካ ይትባህል ዛሬም ከትናንቱ በባሱ የፖለቲካ ደናቁርትና ምንደኞች ሳይላቀቅ ሦስት አሥርተ ዓመታት አልፈውታል። ታዲያም ከትናንት የዋህ የለብለብ ካድሬዎች የዛሬዎቹ ሲነፃፀሩ አንዳንዴ ገራገሮች ባይጠፉም፤ በአብዛኛው ግን ’እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል’ አለች እንደተባለው እንስሳ ሆዳቸውን ያስቀድሙና ዓይናቸውን በጨው አጥበው በድርቅና ጥፋት መሆኑን አውቀው ለጥቅም የተሰማሩ ’የአባትህ ቤት ሲፈርፍ አብረህ ዝረፍ’ የሚለውን ሠይጣናዊ ጥቅስ መመሪያ በማድረግ፤ የሀገር ውድቀት የህዝብ ጉስቁልና ዋይታና ሰቆቃ አይተው እንዳላዩ በመምሰል በወገናቸው ላይ ለሚፈፀመው ኢ-ፍትሃዊ ተግባር ተባባሪ በመሆን የተሰማሩ ካድሬዎችና ለዚህ የግፍ ተግባር ለመሰማራት የሚቋምጡ ጭፍሮች በሀገርም በውጭው ዓለምም እየተበራከቱ በመሄድ ላይ ናቸው። ... (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
Banner

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ