የረቡዕ ግጥሞች Print E-mail
User Rating: / 28
PoorBest 

ቁጥር ፩

አሁንስ በዛ የኔ ችግር

መነጽር ፍለጋ ሌላ መነጽር

ይህስ አልመሰለኝም የዓይን

ሰውሮኝ ነው ህሊናዬን

 

ቁጥር ፪

መሄጃ መች አጣሁ ወደሷማ

ሞልቶኛል ብዙ ጫማ

አልገባችሁም ነገሩ

ተሸፋፍኖ ነው ፍቅሩ።

 

ቁጥር ፫

እገደል አፋፍ ዛፍ በቅሎ

ለቆረጣ አልመች ብሎ

ዘመድ አዝማድ በአንድነት

እንክበደው ብሎ ወጣበት

ዛፉ ተገንድሶ ወደቀ

የ‘ንክበደው ዘርም አለቀ

 

ቁጥር ፬

ለምን ትላለህ ሰው ጠፋኝ

መጀመሪያ እራስህን አግኝ

አንተን አግኝተህ ስታበቃ

ሌላ ሰው ፈልግ በቃ።

 

ቁጥር ፭

እኔ ክፉ ሆንኩ በል ወንድሜ

እኔን አትጥራኝ አለስሜ

ሰው ከፋ ብለህ ጠልተከኝ

ከኔ ፍቅር አትመኝ።

 

ቁጥር ፮

ሲበርደን ኡ ኡ ታ

ሲሞቀን ኡ ኡ ታ

ሲርበን ኡ ኡ ታ

ስንጠግብ ኡ ኡ ታ

ስንጠማ ጩኸት

ስንጠጣ ጩኸት

ስንፋቀር ጩኸት

ስንጣላ ጩኸት

በድለንም ለቅሶ

ሲበድሉን ለቅሶ

ግራ ግብት አለው

እግዜሩ ጨርሶ


ወለላዬ ከስዊድን This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

 

ተያያዥ

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!