ቁጥር ፩ አሁንስ በዛ የኔ ችግር መነጽር ፍለጋ ሌላ መነጽር ይህስ አልመሰለኝም የዓይን ሰውሮኝ ነው ህሊናዬን ቁጥር ፪ መሄጃ መች አጣሁ ወደሷማ ሞልቶኛል ብዙ ጫማ አልገባችሁም ነገሩ ተሸፋፍኖ ነው ፍቅሩ። ቁጥር ፫ እገደል አፋፍ ዛፍ በቅሎ ለቆረጣ አልመች ብሎ ዘመድ አዝማድ በአንድነት እንክበደው ብሎ ወጣበት ዛፉ ተገንድሶ ወደቀ የ‘ንክበደው ዘርም አለቀ ቁጥር ፬ ለምን ትላለህ ሰው ጠፋኝ መጀመሪያ እራስህን አግኝ አንተን አግኝተህ ስታበቃ ሌላ ሰው ፈልግ በቃ። ቁጥር ፭ እኔ ክፉ ሆንኩ በል ወንድሜ እኔን አትጥራኝ አለስሜ ሰው ከፋ ብለህ ጠልተከኝ ከኔ ፍቅር አትመኝ። ቁጥር ፮ ሲበርደን ኡ ኡ ታ ሲሞቀን ኡ ኡ ታ ሲርበን ኡ ኡ ታ ስንጠግብ ኡ ኡ ታ ስንጠማ ጩኸት ስንጠጣ ጩኸት ስንፋቀር ጩኸት ስንጣላ ጩኸት በድለንም ለቅሶ ሲበድሉን ለቅሶ ግራ ግብት አለው እግዜሩ ጨርሶ
ወለላዬ ከስዊድን
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
|
|