ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም በዓይናችን አሳየን (ብርዞ)
 
በዓይናችን አሳየን (ብርዞ) Print E-mail
User Rating: / 1
PoorBest 

በዓይናችን አሳየን

ብርዞ ከፍራንክፈርት This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it  

ኅዋ ድረስ ያመጠቀን ጥዑመ ዜማ ቅኝት

ድንበሩን ጥሶ ያለፈ የማይታዘዝ ለምድር ስበት

በስሜት ተውጦ አካልህ ሲፈነዳ ተመንጭቆ

ልሳንህ በኛ ላይ ገዝፎ ስነልቦናችን ተሰርቆ

ሲታደስ በዜማህ ነፍሳችን ሲርመሰመስ በደማችን

የፈቃድ ሞት እየሞትን በመድረክ ድል ተደርገን

ተቃኝቶ ተቀናብሮ መሣሪያው ሲያስተጋባ

እንደ አውሎነፋስ ተሽከርክሮ በጆሮአችን ሲገባ

ጣዕመ ዜማህ ሲንቆረቆር ቆልምመህ ስትንሳፈፍ

ከመስማት አልፎ አየነው ሕይወት አግኝቶ ሲከንፍ

ምዕተ ዓመት የሰው ልጅ ዜማን ሲሰማ ቆይቶ

እንድናይ አረገን ማይክል በአካሉ ኖታውን ሠርቶ

ፀሐይ ግለትዋን አውሳህ አዝጋሚ ጉዞን ጨረቃ

በማይታመን ተሰጥዖህ መሬት አንተን አድንቃ

እያየ ኪነ ተዓምር ፍጡር ተወልዶ ሲከስም

እየመሸ እየነጋ እስከወዲያኛው ዝንተዓለም

ፈቃድዋ እስካለ ምድር በሰው መኖሪያነትዋ

የማይደገም አቀንቃኝ ማይክል ይሆናል አንደበትዋ

ነፍስህ ፀጋን ትታደል የማያልቀውን የገነት

የአቢሲኒያ ምርኮኞችህ ያስታውሱሃል በፀሎት

ለጋሽ ጥላሁን አድርስልን የከበረውን ሠላምታ

ከኛ ጋር አብሮ አለ በዕለት ተለት ትውስታ


 

ለማይክል ጃክሰን መታሰቢያ

ብርዞ ከፍራንክፈርት This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it  

 

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!


በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ