|
በዓይናችን አሳየን ብርዞ ከፍራንክፈርት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
ኅዋ ድረስ ያመጠቀን ጥዑመ ዜማ ቅኝት ድንበሩን ጥሶ ያለፈ የማይታዘዝ ለምድር ስበት በስሜት ተውጦ አካልህ ሲፈነዳ ተመንጭቆ ልሳንህ በኛ ላይ ገዝፎ ስነልቦናችን ተሰርቆ
ሲታደስ በዜማህ ነፍሳችን ሲርመሰመስ በደማችን የፈቃድ ሞት እየሞትን በመድረክ ድል ተደርገን ተቃኝቶ ተቀናብሮ መሣሪያው ሲያስተጋባ እንደ አውሎነፋስ ተሽከርክሮ በጆሮአችን ሲገባ ጣዕመ ዜማህ ሲንቆረቆር ቆልምመህ ስትንሳፈፍ ከመስማት አልፎ አየነው ሕይወት አግኝቶ ሲከንፍ ምዕተ ዓመት የሰው ልጅ ዜማን ሲሰማ ቆይቶ እንድናይ አረገን ማይክል በአካሉ ኖታውን ሠርቶ ፀሐይ ግለትዋን አውሳህ አዝጋሚ ጉዞን ጨረቃ በማይታመን ተሰጥዖህ መሬት አንተን አድንቃ እያየ ኪነ ተዓምር ፍጡር ተወልዶ ሲከስም እየመሸ እየነጋ እስከወዲያኛው ዝንተዓለም ፈቃድዋ እስካለ ምድር በሰው መኖሪያነትዋ የማይደገም አቀንቃኝ ማይክል ይሆናል አንደበትዋ ነፍስህ ፀጋን ትታደል የማያልቀውን የገነት የአቢሲኒያ ምርኮኞችህ ያስታውሱሃል በፀሎት ለጋሽ ጥላሁን አድርስልን የከበረውን ሠላምታ ከኛ ጋር አብሮ አለ በዕለት ተለት ትውስታ
ለማይክል ጃክሰን መታሰቢያ ብርዞ ከፍራንክፈርት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
|