Home ኪነ-ጥበብ ግጥም እሽሩሩ (አስፋወሰን ዓለምሰገድ)
እሽሩሩ (አስፋወሰን ዓለምሰገድ) Print E-mail
User Rating: / 0
PoorBest 
Art - ግጥም Poem

እሽሩሩ

አስፋወሰን ዓለምሰገድ This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it

እሽሩሩ ...

እሽሩሩ ...

እሽርሩ ማሙዬ ...

ልንከባከብህ ’እሽሩሩ ...’ ብዬ

አባት ሆኛለሁ በተራዬ።

 

የአባቴን ፍቅር ባንተ አየሁት

የፍቅሩን መጠን ተረዳሁት

በል እንግዲህ እደግልኝ

የአባቴ ምትክ ስለሆንከኝ።

ስታለቅስብኝ ምርር ብለህ

የሚናገር አፍ ስለሌለህ

ይጨንቀኛል ይጠበኛል

የማደርገው ይጠፋኛል።

 

ስትስቅልኝ እኔን አይተህ

ባባትነቴ ተደስተህ

ልቤ በኀሴት ይፈነድቃል

ለካ ከልጅ ደስታ ይገኛል።

ልመርቅህ ማሙሽዬ

ለወግ ለማዕረግ ያብቃህ ብዬ

እኔ አባቴን እንደተካሁ

አንተም እኔን እንድትተካ እመኛለሁ።

 

ልጅ ፍቅሬ እባክህን

እናፍቃለሁ ፈገግታህን

ጉንፋን እንኳን እንዳይዝህ

እመኛለሁ እኔ አባትህ።

 

አባቴ ይወደኝ ነበር በልጅነቴ

ሳይቀየመኝ በጥፋቴ

እኔም በተራዬ እንደ አባቴ

በልጄ ፍቅር ጋየ አንጀቴ።

ልጅ ለካ የደስታ ምንጭ ነው

አወይ! ቀርቶብኝ እስከ ዛሬ ሳላውቀው።


 

”ፀሐይ ትወጣለች” ከተሰኘው የግጥም መደብል የተወሰደ

መጽሐፉ የታተመው July 2008

አስፋወሰን ዓለምሰገድ This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it

 
 

Memorial for Abune Zena Markos

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ