ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም የኀዘን እንጉርጉሮ (አስፋወሰን ዓለምሰገድ)
 
የኀዘን እንጉርጉሮ (አስፋወሰን ዓለምሰገድ) Print E-mail
User Rating: / 4
PoorBest 

የኀዘን እንጉርጉሮ

አስፋወሰን ዓለምሰገድ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

 

ከሰባ ዓመት በፊት በየካቲት ወራት

ከጣሊያን የመጣው ቀዳማዊው ፋሽስት

አሥራ ሁለት ሺ ሰው የጨፈጨፈባት

አዲስ ከተማችን ዛሬስ መቼ አደላት

መለስ የተሰኘው ዘመናዊው ፋሽስት

በአሥራ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት

ሳይለይ ሽማግሌ ህፃን እና ወጣት

በጠራራው ፀሐይ በጥይት ሰዋባት።

 

ለዛች ምስኪን እናት ምን ብዬ ልንገራት?

ልጅሽ ሞተ እንዳልል አያውቅም ታሞባት

እንደ ወጣ ሲቀር ወያኔ ቀስፎባት

ኧረ እኔስ ጨነቀኝ እንዴት ብዬ ላርዳት?

 

ወንድምህ ተመትቶ ሊሞት ነው ሲሉህ

እየበረርክ ስትሄድ ስጋ ሆኖብህ

ወያኔ ጨካኙ ትንሽ የማይራራ

አንተንም ቀሰፈህ ከወንድምህ ጋራ።


 

ከግንቦት 1997 ምርጫ በኋላ በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የተጻፈ

”ህዝባችንን ልቀቅ” ከተሰኘው የግጥም መደብል የተወሰደ

መጽሐፉ የታተመው Sepetember 2005

ደራሲ - አስፋወሰን ዓለምሰገድ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

 

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!


በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ