Home ኪነ-ጥበብ ግጥም የቴዲ አፍሮ ፀሎት በእስር ቤት (አስፋወሰን ዓለምሰገድ)
 
የቴዲ አፍሮ ፀሎት በእስር ቤት (አስፋወሰን ዓለምሰገድ) Print E-mail
User Rating: / 3
PoorBest 
Art - ግጥም Poem

የቴዲ አፍሮ ፀሎት በእስር ቤት

አስፋወሰን ዓለምሰገድ This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it

 

ኢትዮጵያን ማፍቀሬ ወንጀል ሆኖብኝ

አንድነት ማፍቀሬ ጥፋት ሆኖብኝ

እየፎከሩ ነው በሞት ሊቀጡኝ፤

ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር ሆነህ ከዙፋንህ

አንተስ በእነሱ ላይ ምን ይሆን ቅጣትህ?

 

እግዚአብሔር ሆይ እጄን አንስቼአለሁ

ፍርድህን አታዘግይ ብዬ እማጸናለሁ።

 

ፍቅርን በዘራሁ በጸብ አውድማ ላይ

ሠላምን ባሳደግሁ ኃይማኖትን ሳለይ

እነሆ ተገረፍኩ በሐሰት ጅራፍ

በእስር በስቃይ ነፍሴ እንድታልፍ።

 

የሠራዊት ጌታ ኢትዮጵያን ታደጋት

ከጭካኔ አገዛዝ እባክህ ነፃ አውጣት።

ለአንተ አንመችም ይህንን አውቃለሁ

በፀጋ ታደገን ብዬ እጮሃለሁ።

 

ለብዙ ዘመናት ቃል ገብተህልን

በነፃነት ጥላ በድል መርተኸን

ዛሬ ምነው ጌታ ለስቃይ ዳረከን

እኛን በመሰሉ ፍዳ አስቆጠርከን።

 

እግዚአብሔር ሆይ! እባክህ ኢትዮጵያን አትርሳት

ከሰማየ ሰማያት ሠላምን ላክላት።

ህዝቦችዋ ተባብው በፍቅር በሐሴት

ለመኖር አብቃቸው በእውነተኛ ሕብረት።

 

እኔስ ልኑር በቃ በእስር በግዞት

ሱባዔ ገብቼ ለሀገሬ አንድነት።

ምህላዬን እባክህ በፍጥነት ስማኝ

ህዝቤን ሳትዘገይ ነፃ አውጣልኝ።

 

ፀሐይ ትወጣለች‼!


አስፋወሰን ዓለምሰገድ 01/05/2009 This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it

 

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ