ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም ለብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የ፵ ቀን መታሰቢያ
 
ለብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የ፵ ቀን መታሰቢያ Print E-mail
User Rating: / 9
PoorBest 

ለብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የ፵ ቀን መታሰቢያ

አቤል አድማሱ

ሰው ጠፍቶብኝ ስባዝን

ተወዳጁን ወገኔን

የኦርቶዶክስ ጠበቃን

የሀገር ቅርስ አቡኑን

የትህትናው አባቴን

ምስክሬ እድገቴን

ኢትዮጵያዊው አድባሬን

ዜና ማርቆስ ታላቁን

ባለ ማዕረግ ጳጳሱን

ከላይ ከታች ባዘንኩና

ላላገኘው እንደገና

ተስፋ ሳልቆርጥ እንድፀና

ያንን መልካም ባለዝና

አባታችን ወዴት ነህ?

ዜና ማርቆስ ወዴት ነህ?

ብንመጣ ያጣንህ

አልነበረም ልማድህ

ሰው ሲመጣ መሸሽህ

ጤና አጥቷል ብለውኝ

ይማር ብዬ ማለድኩኝ

አሁንማ ፈራሁኝ

ዝም እንዳልል ባባሁኝ

ለካ እውነት ነው መጥፋትህ

ውሎ አድሮ መሄድህ

ሰው ነህና ደረሰህ

ተስፋ ቆረጥኩ ከእንግዲህ

ዜና ማርቆስ ታላቁ ሰው

ትህትናን ያስተማርከው

መልካም ትምህርት ያበሰርከው

ዜና ማርቆስ የወንጌሉ

መምህራችን ርዕቱ ቃሉ

ተባረክን በመስቀሉ

ተፈወስን በፀበሉ

ቀድስልን እባክህ

ስበክልን እባክህ

አስተምረን እባክህ

ዜና ማርቆስ ባባትህ

በአዛኝቱ በናትህ

አንተማ ሄድክ እንደዋዛ

ሀዘናችን በጣም በዛ

አንተማ ሄድክ በቀላል

አንጽተኽን ከበቀል

እግዜር ያጥናሽ ኢትዮጵያ

አጣሽ አሉ ሐዋርያ

እግዜር ያጥናሽ ተዋኅዶ

ሊቅ ሞተብሽ በተለምዶ

እግዜር ያጥናህ ሉቃስን

ዮሐንስን አቡኑን

ካህናትን ምዕመናን

አትቀስቅሱት ያንን ሰው

ጸሎት ምልጃው ለኛ ነው።


የአባታችን በረከትና ጸሎት በሁላችን ላይ ይደርብን!

አቤል አድማሱ

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!


በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ