ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም አልነጋም- ገና ነው! (ዳግማዊ ዳዊት)
 
አልነጋም- ገና ነው! (ዳግማዊ ዳዊት) Print E-mail
User Rating: / 4
PoorBest 

አልነጋም- ገና ነው!

ዳግማዊ ዳዊት This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

የሰማይ ኮርኒሥ ሆኖ - ማቅ የመሰለ ደመና

ከታችም አውሎ ነፋስ - ፉጨቱን እያሰማ

አቧራውን አስነስቶ - ዛፍ ቅርንጫፉን እያሾረ

ዛሩ እንደወረደ ባለአውሌ - አለመጠን እያስጨፈረ

ዓይን ቢወጉ በማያሳይ - ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ

ወዴት ነው መድረሻችን - ጉዟችን የሚያቀና?

 

ትናንት እንዳስቆመን ዝናብ - ሊዘንብ ሰማዩ አግቶ

ወዴት ነው የምንሄደው - በትናንቱ ምን ታይቶ?

 

ትርምስምሳችን ወጥቶ - ጨቅይቶ ሳለ መንገዱ

ለይምሰል አይሆንም ወይ - ደግመን ዛሬ መሄዱ?

 

ትናንት መካሪ ጠፍቶ - ሌሊቱ ገና እንዳልነጋ

ጉዞው መርዛም - እሾክ በዝቶበት - ስንቱ ነው የተወጋ?

 

እኔስ አልምክርውም- የዛሬውን መንገድ

እስኪነጋ እቆያለሁ - ካልሆነብኝ የግድ

አልነጋም ገና - ጨለማ ነው ሌሊት

እነሱንም ንገሩዋቸው - መጓዙን ይተዉት

ተከታያቸውን በመሉ - የአውሬ ቀለብ አያርጉት።


ዳግማዊ ዳዊት

This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

ጥር 2002 ዓ.ም.

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!


በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ