|
አልነጋም- ገና ነው! ዳግማዊ ዳዊት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
የሰማይ ኮርኒሥ ሆኖ - ማቅ የመሰለ ደመና ከታችም አውሎ ነፋስ - ፉጨቱን እያሰማ አቧራውን አስነስቶ - ዛፍ ቅርንጫፉን እያሾረ ዛሩ እንደወረደ ባለአውሌ - አለመጠን እያስጨፈረ ዓይን ቢወጉ በማያሳይ - ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ ወዴት ነው መድረሻችን - ጉዟችን የሚያቀና?
ትናንት እንዳስቆመን ዝናብ - ሊዘንብ ሰማዩ አግቶ ወዴት ነው የምንሄደው - በትናንቱ ምን ታይቶ? ትርምስምሳችን ወጥቶ - ጨቅይቶ ሳለ መንገዱ ለይምሰል አይሆንም ወይ - ደግመን ዛሬ መሄዱ? ትናንት መካሪ ጠፍቶ - ሌሊቱ ገና እንዳልነጋ ጉዞው መርዛም - እሾክ በዝቶበት - ስንቱ ነው የተወጋ? እኔስ አልምክርውም- የዛሬውን መንገድ እስኪነጋ እቆያለሁ - ካልሆነብኝ የግድ አልነጋም ገና - ጨለማ ነው ሌሊት እነሱንም ንገሩዋቸው - መጓዙን ይተዉት ተከታያቸውን በመሉ - የአውሬ ቀለብ አያርጉት።
ዳግማዊ ዳዊት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
ጥር 2002 ዓ.ም.
|