እርጉዟ ሚስቴ ዳግማዊ ዳዊት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
ቀረ አልቀረ ሚስቴ - በዚህ ወር አርግዛ አማረኝ ትላለች - ፍትህ እንደዋዛ ጠዋት ከእንቅልፍ ነቅታ - ምሬት ምሬት ሲላት ምግብ አይበላት - ውሃም አይጠጣት ምን ላቅርብ ምን ላምጣ- ብዬ ስጠይቃት አንድነት ትላለች - ነፃነት በፍትህ ብቻየን አልጥድህ - ፍትህ ከየት ላግኝህ? “ሙያ ዱሮ ቀረ” ትለኛለች አዝና ጠይቃኝ ሳላገኝ - ፍትህ እንደገና “ያኔ ዱሮ ዱሮ - አባቴ ተረግዘው እማሆይ አያቴ - ፉከራ ሲያምራቸው ዘራፍ ሲሉ አባባ - የአባ ዳኘው አሽከር ግርማው የአባ በዝብዝ - ሙያው ያምር ነበር አንተማ የኔ ባል - ባሌ የተባልከው ፍፁም አላየኸው - ሙያውን አታውቀው ዘራፍ አትል አንተ - ፍፁም አልዋልክበት እኔ ባለሁበት - አንተ እየኖርክበት ማን ይበል ይፎክር - ዘራፍ ይበል ወንዱ አብረን መዋላችን - አይደልወይ ገሃዱ ትናንት ጀምሬ - ጠይቄ እርጉዝ ሚስትህ አማረኝ እያልኩህ - ነፃነት በፍትህ ሙያ በአንተ የለም - ባንተስ ወንድነትህ” ብላ ወንድነቴን - ፈተና ከታው ጉድ ሆኛለሁ ዛሬ - እንዴት ልወጣው? እኔ ደካማው ባል - ጀግንነት የሌለኝ ሚስቴ ያማራትን - ማቅረቡ ተሳነኝ። የትናንት ጀግንነት - የአባቶች ወንድነት መተባበር ነበር - መታገል በአንድነት ዛሬ የኔ ትውልድ - አንድነት አቅሮት ኑሮውን ይገፋል - በኀዘን በምሬት። ማቅረብ እኔ እንድችል - ሚስቴ ያማራትን ከሁላችን በፊት - ትቅደም ሀገራችን ፍፁም አይጠቅመንም - መለያየታችን እስኪ ሁላችንም - እኛኑ እንይና ምን እንደሚጎለን - እንመርምርና እንታገል ትግልን - አንድ እንሁንና።
ዳግማዊ ዳዊት
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
ነሐሴ 2001 ዓ.ም. |