ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም ቆሜ ነው እምሞተው !! አሥራደው (ከፈረንሳይ)
 
ቆሜ ነው እምሞተው !! አሥራደው (ከፈረንሳይ) Print E-mail
User Rating: / 7
PoorBest 

አልጠብቅም ሞትን ተኝቼ ባልጋዬ ፤

እኔው እሄዳልለሁ ፈረሴን ቼ ! ብዬ ፤

በ’ንባ አልታጠብም ቁጭ ብዬ አላለቅስም ፤

ጉልበቴን አጥፌ አልንበረከክም ፤

አልጠብቅም እሱን ወደኔ እስቲመጣ ፤

እኔው እሄዳለሁ ወደሱ እንዳይመጣ ፤

ኩራቴን ይረዳው ድፍረቴን ይወቀው ፤

ተጋድሜ አልሞትም ቆሜነው እምሞተው !!


አልፈልግም ዋሻ የምደበቅበት ፤

አያሻኝም ጢሻ የምሸሸግበት ፤

አልሰብርም አንገቴን አላዞርም ፊቴን ፤

አይዝልም ጉልበቴ አላጥፈውም ክንዴን ፤

እጠብቀዋለሁ ደረቴን ነፍቼ ፤

በኩራት በድፍረት ጋሻዬን መክቼ ፤

አልንበረከክም ቆሜነው እምሞተው ፤

የጀግና ልጅ ጀግና መሆኔን ይወቀው !!

አልጠብቅም ሞትን ማታ በጨለማ ፤


እንዲወስደኝ ብዬ ሰው ሳያይ ሳይሰማ ፤

አለምንም ከቶ ዛሬን እንዲተወኝ ፤

ዘግይቶ እንዲመጣ ዕድሜ እንዲለግሰኝ ፤

ያልጋ ቁራኛ አርጎ እያጨማለቀ፤

ሞት መጥቶ እስቲወስደኝ እያመናጨቀ ::

ጭራሹን !

እጠብቀዋለሁ በጠራራ ፀሐይ ፤

መሃላዬ ይሁን ቃል ለምድር ለሰማይ ፤

ቆሜነው እምሞተው እንደ ክርስቶስ

ዳግም ድል አድርጌ እስክነሳ ድረስ ::


ይጥልልኝ ብዬ ትርፍራፊ እድሜ ፤

አልጠብቅም ሞትን እኔ ተጋድሜ ፤

እሄዳለሁ እኔ ወደሱ እንዳይመጣ ፤

ግንባሬን አላጥፍም የመጣው ቢመጣ ፤

ተኝቼ አልጠብቅም ሞት መጥቶ እስቲወስደኝ ፤

እኔው እሄዳለሁ በቁሜ እንዲያገኘኝ ፤

ለመኖር ጓጉቼ አልንበረከክም ፤

ዛሬን ተወኝ ብዬ አልለማመጥም ፤

አልንበረከክም ቆሜነው እምሞተው ፤

የጀግና ልጅ ጀግና መሆኔን ይወቀው !!

አንድ ቀን

ለወጣት መምህር የኔሰው ገብሬ :

እንዲሁም ፤

የአገራቸውን ውድቀት፤ የወገናቸውን ድቀት፤ እንቢ በማለት : ለእኩልነት፤ ለአንድነት፤ ለዲሞክራሲና ለፍትህ መከበር በመታገል ለወደቁ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን በሙሉ መታሰቢያ ትሁንልኝ ::

To Remember the young Ethiopian Teacher Yenesew Gebré and  Ethiopian Martyrs of June and November 2005.

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
Banner

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ