ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም እንበል አስራ ሰባት (እንቆጳ)
 
እንበል አስራ ሰባት (እንቆጳ) Print E-mail
User Rating: / 6
PoorBest 

እንበል አስራ ሰባት*

ከእንቆጳ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

ከጨለማው በስተጀርባ

ከድቅድቁ ብርሃን አልባ

ከጣይቱ መውጫ ማዶ

ሰው አየሁኝ ዛሬ ማልዶ።

የጥቁር ዘር አፍሪቃዊ

የኩሽ ቅሬት ነባራዊ

የበቀለው ካገሬ-አፈር

የሜቶ ልጅ የብርቱ ዘር።

እንደተወጣው ሽቅቡን

የቅኝ ግዛት አቀበቱን

አባ ዳኘው ዛሬም ከርሞ

ሞተ ስንል ነቃ ደግሞ

ስብዕናን አገልድሞ።

የወንዜ ልጅ ጊቤ-ባሮ

የአኟክ ፍሬ ከኩሽ ጓሮ

ዛሬም ያፈራል ደግ-ደጉን

የምዬ ሆድ ወንድም ክንዴን

ሩቅ አላሚ አሳቢዋን እታለምን።

ታየ! ሰው ታየ! ከዚያ መንደር

ለወገን ስንቅ ጥላ ላገር።

ፍትህ ናፍቆት እንደብርቱ እንደህቱ

ፍቅርን ሰብኮ በጠዋቱ

አለ ዘሬን ከስር ፍቱ!!


*ሰሞኑን በአቶ ኦባንግ ሜቶ አማላጅነት ከጃፓን እስር ቤቶች ለተፈቱት 17 ስደተኛ ኢትዮጵያውያን፤

ከእንቆጳ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
Banner

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ