|
አዛለች ወደ ፓርላማ (የምርጫ ጭውውት) ክፍል ሦስት ዳግማዊ ዳዊት ባላፈው መጋቢት - የአቦለት ቤተክሲያን ጠጋ ብዬ ጠየቅሁ - ወረቀት ሲበተን እንዲህ ይነበባል - በራሪው ወረቀት ከላይ ምርጫ ብሎ - ከታች ንብ አለበት፤
አዛል ምርጫ ገባች- ሹርባ ተሰርታ መረራ ጉዲናን - በድምፅ ልትረታ
ኢህአዴግ ፓርቲዋን - ወክላ ቀርባለች ልማታዊቷ ሴት ምረጡኝ - ትላለች። ፎቶውን አይቸ - አንገቴን አቅንቸ መፈለግ ጀመርኩኝ - አዛሉን ጓጉቸ። መስቀል ሲሳለሙ - አየኋችውና - ለብሰው ጃኖ ኩታ መንገዴን ቀጠልኩኝ - ከቆሙበት ቦታ።
“ዶ/ር አዛሉ! ዶ/ር …” - ብዬ ስጠራችው የፌደራል - ፖሊስ ወገቤን ዠለጠው “አተ… አታ ባለጌ” - ብሎ ሲጮህብኝ መሬት ተሰንጥቃ - ትውጠኝ ተመኘሁኝ። እኝህማ አዛሉ - እኔ የማውቃቸው ጠላ ኮማሪዋ - አይደሉ እንዴ እሳቸው።
ፖሊስ ቢዠልጠኝ - በያዘውም ዱላ ምን ሊባል - ይገባል ከብልግና ሌላ እንዲህ ያለ - ጥሪ “ዶክተር!” ብሎ ማለት ስድብ ብቻ ሳይሆን - ብልግናም አለበት ከአንድም ሁለት ጊዜ - ለቀበሌ ሸንጎ ራቦል ጥፌያልሁ - ለአዛለች ሽመኮ
ማንበብና መፃፍ - የማያውቁትን ሴት ዱላ እማይበቃው ነው - ዶክተር ብሎ መጥራት ፖሊስ አዋከበኝ - ዶለኝ ወኸኒ ቤት አዋርዷል ተብዬ - ልማታዊቷን ሴት። ************
ሁለት ወር ታስሬ - የተፈታሁኝ ቀን አሸነፉን ሰማሁ - አዛሉ መረራን። የሰፈራችን ሹም - የወያኔው ኔጭ ሹም እንዲህ አርጎ አሰማኝ - መቸም ጉድ አያልቅም።
“የሰፈር ወይዘሮ - የጠላ ኮማሪ የትናንት ልማት ሴት - ሥራን አስተማሪ ማንበብ መጻፍ ባይኖር - ማይምም ቢሏቸው ሀገር መገንባትን - ዲሞክራሲ አውቀው የመንግሥት አመራር - በደንብ ገብቷቸው አዛሉ ዶከተሩን - ጥለው አሳይዋቸው ፖለቲካ ሳይንስ - ዓለም አቀፍ ቢሉ ዶክተር መረራ ነኝ - የታወቅሁት ቢሉ መረራ ተረታ - ድል ሆነ በአዛሉ።
ወይዘሮ አዛለች ነች - የሆነች አንበሳ እንግዲህ በጀ በል - አምቦም እጅ ንሳ። አሜሪካን ሀገር ያለሽው ሂላሪ ይልቅስ ነይና - ከአዛለች ተማሪ።” በስጨትጨት ብየ - እልሄ መጣና መናገር ጀመርኩኝ - ተራዬ ሆነና። “ገና ዱሮ ነበር - ያኔ ሳይወጠን አልነጋም ያልናቸው - የዛሬውን አይተን። መለስ ወንፊት ሰፍቶ - ማበጠር አቅዶ ልደቱ እህል ሆኖ - ኃይሉም ገብቶ ወዶ ይኸው ተበጠረ - መረራም ወረደ ግፍም ሕግ ሆነና - ውሸት ተለመደ።”
ብዬ ተናግሬ - ልጨምር ስሞክር ስውር ፖሊስ ኖሮ - ከነጭ ለባሹ ጋር ሽጉጡን አውጥቶ - እያንገራገረ - ማጅራቴን ይዞ እስር ቤት ጨመረኝ - በመኪና አግዞ።
ዳግማዊ ዳዊት ግንቦት 2002
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
|