ዋና ገጽ ኪነ-ጥበብ ግጥም ”ኖረ” (ፊልጶስ)
 
”ኖረ” (ፊልጶስ) Print E-mail
User Rating: / 6
PoorBest 

”ኖረ”

ፊልጶስ ከሆላንድ

በልቶ ጠግቦ አደረ ምንም ሳይርበው

ወይም አልጠግብ ባይ ቁጣን አመመው

ጠፍቶ የሚቀምሰው ወይም ጠኔ ጣለው፤ …

ሲቀረሻ ዋለ ካላቅሙ ጠጥቶ

ወይም ደርቆ ዋለ ጉሮሮው ውሃ አ’ቶ፤ …

ምርጥ - ምርጥ ለበሰ እጅግ አማረበት

ወይ እርቃኑን ሄደ ቡቱቶው አልቆበት፤ …

ሲፈነጥዝ ታየ ደስታ ፈነቀለው

ወይም ኀዘን ችግር ባልንጀራ አ’ረገው፤ …

ህሊናውን ሸጦ - ላላፊ ጥቅም ለውሸት አደረ

ከሕግ በላይ ሆኖ በሥልጣን ባለገ - ፍትህን አሰረ

ወይ ሳያወላውል ጊዜ ሳይለውጠው ከእውነት ጋር አበረ

በአግባቡ ፈረደ - ትህትናን ተሞልቶ ህዝብን አከበረ፤ …

በቁሙ የሚሞት - እየሞተ እሚኖር ፈሪ ሆነ ‘ርብትብት

ወይም ቆራጥ ጀግና ባላማው የፀና - የማይፈራ ሞት፤ …

ት’ግስተኛ አዋቂ እጅግ ደግ የዋህ ነው - የለበሰ ፍቅርን

ወይም ”ጠብ ያለሽ በዳቦ” ችኩል ጨካኝ ይሁን፤ …

ብቻ … በምድር ላይ እስትንፋስ ካለው

እንደ አፈጣጠርም ሥራም ዥንጉርጉር ነው

ከመሸም ከነጋ ውሎ ካደረ ሰው

ስሙ መጠሪያው ለሁሉም የወል ነው

ጥንትም ሆነ ዛሬ ”ኖረ” ነው እሚባለው።


 

ፊልጶስ ከሆላንድ This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
Banner

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ