|
 Ethiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ በያዝነው የአውሮፓውያን 2009 እየተካሄደ ባለው የኤ.ኤፍ. ጎልደን ሊግ አትሌቲክስ በ5 ሺህ ሜትር ርቀት አትሌት ቀነኒሳ በቀለ እና መሰረት ደፋር በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቀቁ። የጎልደን ሊጉን አንድ ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይቋደሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት አትሌቶች ውስጥ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይገኙበታል።
|
|
Read more...
|
|
“አቶ ስዬ አብርሃ አንድነትን ለመቀላቀል ጥያቄ አላቀረቡም፤ ማመልከቻም አላስገቡም” ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ Ethiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው እሁድ በደብረ ማርቆስ ከተማ ያካሄደው ስብሰባ ብዙ ፈተናዎች ቢያጋጥሙትም በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ። |
|
Read more...
|
|
የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን መንበረ ፕትርክና 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል አከባበር በቤተክህነቱ ግቢ ምጥው ለቤ
This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it
ሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ በመጥራቷ፤ ኃላፊነት ያለባቸው ሊቃነ ጳጳሳት በጉባዔው ላይ ለመሳተፍ ከየሀገረ ስብከታቸው ወደ መንበረ ፓትርያርኩ የእየተሰቡ መገኘታቸው ተደምጧል። ጉባዔው በቤተክህነቷ አካባቢ አለ ለሚባለው አስተዳደራዊ ችግር መፍትሔ ይሰጣል ተብሎ ይገመታል። ይህ ጉባዔ የሚካሄደው ቤተክህነቷ የራሷን ፓትርያርክ በሾመችበት በ50ኛ ዓመት ላይ ነው። ታሪክን አጣቅሶና ጉባዔውን አስመልክቶና “ምጥው ለቤ” የሚከተለውን ጽሑፍ አድርሶናል። መልካም ንባብ! |
|
Read more...
|
|
አባ ጳውሎስ ከ“ሕገ-ወጦች ጋር” አናብርም አሉ Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. July 1, 2009)፦ በደሴ ከተማ ፌደራል ፖሊሶች በክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ በወሰዱት የጭካኔ እርምጃ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሁለት ወደ አራት ከፍ ብሏል። ከስፍራው በተቃውሞ ሰልፉ የተሳተፈች ሴትና የፖሊስ ዱላ ያረፈባት ሴት እንደገለጸችልን ከሆነ አንዱ ሟች ከላሊበላ የመጣ በስንቅ የሕክምና ትምህርት የሚከታተል ወጣት ሲሆን፤ አስከሬኑ ወደቤተሰቦቹ መሄዱን ገልጻለች። |
|
Read more...
|
|
ገዢው ፓርቲ ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ማናከሱን ገፍቶበታል Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ በደሴ ከተማ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እንድትሠራበት ታቅዶበት የነበረው ቦታ ለረዥም ጊዜ ሲያወዛግብ ቆይቶ፤ የከተማው አስተዳደር ባለሥልጣናት ቦታውን ሙስሊሞች ተቃውመውታል በሚል ሥራው ተቋርጦ በድንኳን ሲቀደስበት ከቆየ በኋላ፤ መንግሥት መልሶ ቦታውን ለሌላ አገልግሎት ይዠዋለሁ በማለቱ ዛሬ በደሴ ከተማ ብዛት ያለው ህዝብ የተሳተፈበት ሠላማዊ ሰልፍ እንደተካሄደና ከሰልፉ በኋላ በምዕመናንና በፌደራል ፖሊሶች መካከል ረብሻ መነሳቱን የዓይን ምስክሮች ገለጹ። |
|
Read more...
|
|
ለሕክምና ወደ ውጭ ሄደዋል ተባለ Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ ከአዲስ ብሮድካስቲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያለቀረጥ የገቡ የሕትመት መሣሪያዎችን አላግባብ መጠቀም በሚል ክስ ተጠርጥረው ታስረው በዋስ የተለቀቁት እውቁ የሕግ ባለሙያ አቶ አበበ ወርቄ በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ቢወጣባቸውም፤ ዛሬ በዋለው የፍርድ ቤት ውሎ በሕመም ምክንያት ወደ ውጭ ሀገር በመሄዳቸው ሊቀርቡ አለመቻላቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ። |
|
Read more...
|
|
ስለሺ ዘእንግልጣር
This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it
“የምንታገለው ለመንደር ወይስ ለሀገር? መታገል ያለብን ለሀገር አነድነት ነው፣ ሀገር ከሌለች መንደር አይኖርምና።” አቶ ኦባንግ ሜቶ ‘የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የትብብር ንቅናቄ’ መስራች ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ አተኩሮ ላየው ቅንነቱን ለመረዳት ጊዜም አይፈጅም። በተኮላተፈና ጥርት ባለ አማርኛውም ሆነ አቀላጥፎ በሚናገረው እንግሊዝኛው በጨዋ ኢትዮጵያዊነት ከአፉ የሚወጡት ቃላት ልብ ውስጥ ጠልቀው ይገባሉ። ዘወትር በሄደበት ሁሉ የሚናገረው ኢትዮጵያዊነትን ነው። ሊነግረን የሚፈልገው ልዩነታችንን ወደጎን በመተው እርስ በርሳችን በመነጋገር ችግሮቻችንን እየፈታን አንድነታችንን ማጠንከር እንዳለብን ነው። በዘርና በመሳሰሉት ዛሬ ገዥው ፓርቲ የሚያራምደው የጎሣ ፖለቲካ ውስጥ ገብተን በመዳከር እርስ በርሳችን እንዳንጠላላና እንዳንቀያየም ይማጸነናል። “የነገዪቱ ኢትዮጵያ እጣ ያሰጋኛል፤ ዛሬ ካልተባበርን፣ ኢትዮጵያዊ ነን የምንል ሁሉ እጅ ለእጅ ተያይዘን መሔድ ካልቻልን፣ ነፃና ፍትሕ የሰፈነባት ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለማየት የምንጓጓበትን ጊዜ ያርቅብናል እንጂ አያቀርብልንም” ይለናል ኦባንግ። |
|
Read more...
|
|
Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. June 26, 2009)፦ ይህ ዜና ከመፃፉ ከ7 ደቂቃ በፊት የፖፕ ሙዚቃው ንጉሥ ማይክል ጃክሰን በ50 ዓመቱ ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. (June 25, 2009) ማረፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ ለጉዳዩ ቅርበት ያለው ስሙ በይፋ እንዳይገለጽ የፈለገና በኦፊሴል የማይክልን ሕልፈተ ሕይወት ለመግለጽ ያልተፈቀደለት ግለሰብ፤ ማይክል ጃክሰን በሎስ አንጀለስ ሆስፒታል ውስጥ ማረፉን አረጋግጧል። |
|
Read more...
|
|
Ethiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. June 25, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመድረክ ለምክክር ጋር በጋራ ሊያሠሩ ይችላሉ ተብለው በታመኑባቸው ነጥቦች ላይ በቅርቡ ውሳኔ እንደሚሰጥ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ። |
|
Read more...
|
ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ ከእንግሊዙ “ፋይናንሽያል ታይምስ” ጋዜጣ (የጁን 23, 2009 ዕትም) የአፍሪካ ዴስክ አዘጋጅ ዊልያም ዋሊስ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ባደረጉት ቃለምልልስ፤ በኢትዮጵያ በፈቃድ ሥልጣን የመልቀቅ ባህልን መስበር እንደሚፈልጉና የመጀመሪያው በፈቃደኝነት ሥልጣኑን ለቀቀ የሀገሪቱ መሪ ለመሆን እንዳቀዱ ገልፀዋል። በርካታ ኢትዮጵያውያን የጠ/ሚ/ሩን አባባል በጥርጣሬ ከመመልከታቸውም ባሻገር “ሐሰት ነው” የሚል እምነት እንዳላቸው ይታመናል። ይኸው ቃለምልልስ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ስለታሰሩት፣ በፀረ-ሽብር ረቂቅ ሕጉ፣ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ... ጉዳዮች ላይ አተኩሯል። ቃለምልልሱን በሀገር ውስጥ የሚታተመው “ሪፖርተር” ጋዜጣ እንደሚከተለው ወደ አማርኛ ተርጉሞታል። መልካም ንባብ!
|
|
|
Read more...
|
|
|
|
Page 1 of 67 |