Home
ግንቦት ሰባት የተጠራው ሰልፍ በስቶክሆልም ተካሄደ PDF Print E-mail
Thursday, 15 May 2008 13:53

በማትያስ ከተማ

Ginbot 7 Rally  - Stockholm, Sweden

Ethiopia Zare (ኀሙስ ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. May 15, 2008)፦ ግንቦት ሰባት ቀን 1997 ዓ.ም. የተደረገውን የዲሞክራሲ ትግል ለማስታወስና በወቅቱ የተሰዉትን ሰማዕታት ለመዘከር በዛሬው ዕለት ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. (ሜይ 15 ቀን 2008) ሊደረግ ታቅዶ የነበረው ሰልፍ በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ተደረገ። በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አዘጋጆቹ ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገለጡ።

Read more...
 
እነዶ/ር ብርሃኑ ነጋ "ግንቦት 7" ንቅናቄን በይፋ አሳወቁ PDF Print E-mail
Wednesday, 14 May 2008 15:07

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 6 ቀን 2000 ዓ.ም. May 14, 2008)፦ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ አምስት የቀድሞ የቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ስላቋቋሙት "ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ" በተሰኘው አዲስ የፖለቲካ ፓርቲን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ኔትዎርክ (ኢ.ቲ.ኤን.) መግለጫ ሰጡ።

Read more...
 
በኀሙሱ ዓለም አቀፍ ሠላማዊ ሰልፍ በስዊድን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይካፈላሉ PDF Print E-mail
Monday, 12 May 2008 22:19

Reported by Matias Ketema

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2000 ዓ.ም. May 13, 2008)፦ በአቶ ኦባንግ ሜቶ የአኝዋክ ጀስቲስ ካውንስል መሪ አነሳሽነት የፊታችን ኀሙስ ተነገወዲያ ሜይ 15 ቀን 2008 እ.ኤ.አ. (ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም.) በመላው ዓለም የሚደረገው ሰልፍ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልምም እንደሚደረግ አስተባባሪው ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጸ።

Read more...
 
በሲያትል ዶ/ር ብርሃኑ ከህዝብ ጋር ያደረጉት ውይይት PDF Print E-mail
Monday, 12 May 2008 10:46

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2000 ዓ.ም. May 12, 2008)፦ ትናንት በአሜሪካን ሀገር ሲያትል ከተማ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በከተማይቱና በአቅራቢያዋ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያኖች ጋር ህዝባዊ ውይይት ባደረጉበት ወቅት "ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚደረግ ትግል የግድ የሚለው የትብብር ጥያቄ" በሚል ርዕስ ረዘም ያለ ንግግር አድርገዋል።

Read more...
 
ዶ/ር ብርሃኑ በቫንኩቨር የተሳካ ውይይት አካሄዱ PDF Print E-mail
Sunday, 11 May 2008 10:22

(ውይይቱን በድምፅ አቅርበነዋል)

'በሞኖፖል የተያዘውን የኢትዮጵያ ሚድያ ከውጭ ሃገር ሆኖ መስበር ይቻላል'  ዶ/ር ብርሃኑ

Dr. Berhanu, Vancouver public meeting 080510

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2000 ዓ.ም. May 11, 2008)፦ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ትናንት ቅዳሜ ግንቦት 3 ቀን 2000 ዓ.ም. ከቫንኩቨር ነዋሪዎች ጋር ያካሄዱት ውይይት የተሳካና ግልጽ ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ የተጀመረው በቀድሞ የአዲስ አበባ የኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፕሬዝዳንት የነበረው ተማሪ ተክለሚካኤል አበበ የዶ/ሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመምህርነት ተግባርና ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጋር የነበራቸውን ቅርርብ፣ በማስተማርና በመማር ሂደት ላይ ያላቸውን ችሎታ በማውሳትና ምስክርነት በመስጠት ነበር።

Read more...
 
የስደተኛውን ፓትርያርክ ዘገባ በተመለከተ አቋማችን፣ ዓላማችን እና መልሳችን PDF Print E-mail
Sunday, 11 May 2008 14:44

“የምናውቀውን እንናገራለን፣ ያየነውንም እንመሰክራለን”  ዮሐንስ ም. 3፥11

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2000 ዓ.ም. May 10, 2008)፦ “የማይገለጥ የተከደነ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለም” ይላል በስደት የሚገኘው ህጋዊ ሲኖዶስ ዜናችንን አስተባብሎ ባወጣው መግለጫ። ሚያዚያ 24 ቀን በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ “ስደተኛው ፓትርያርክ ለእርቅ ወደ ኢትዮጵያ ሊሄዱ ነው” በሚል ርዕስ መዘገቡ አይዘነጋም። በጉዳዩ ላይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች በተለያዩ ድረ-ገጾች እና ራዲዮኖች የበኩላቸውን አስተያየት በመስጠት ዘገባው “ሐሰት ነው” ሲሉ አስተባብለዋል።

Read more...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 20
 

Events

No images