Home

ምርጫው የማይከበርለት ሕዝብ እንዴት “ምረጠኝ” ይባላል? (ሀብታሙ አሰፋ) Print E-mail

ሀብታሙ አሰፋ

የአቶ መለስ አስተዳደር ደጋግሞ እንደተናገረው የ97ቱ ምርጫ እንዳይደገም ቀዳዳዎችን ሁሉ ደፍኗል። እነዚህ ቀዳዳዎች የታወቁ ናቸው። ምርጫ እንዳይኖር የሚያደርጉ የአፈና እርምጃዎችን ነው። ይቃወሙኛል የሚላቸውን ሁሉ በሞትና በእድሜ ልክ እስራት የሚቀጣበት የፀረ-አሸባሪነት ሕግ አውጥቷል። ከዚህ አልፎም ሕጉ በነማን ላይ እንደሚሰራ እነ ጀነራል ተፈራ ማሞ በፈጠራ ወንጀል በዚሁ አዋጅ መሰረት ተፈረዶባቸዋል። በ97ቱ ምርጫ በገለልተኝነት የታዘቡ የሲቪል ማህበረሰቡን የሚወክሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ፀጥ የሚያደርግ አዋጅ ወጥቷል። የፕሬስ ነፃነት ተስፋ ጭምር እንዲጨልም የዘጋውን ዘግቷል። ያሰጉኛል የሚላቸውንም የቀሩትን ለይቶ ተራ በተራ ለመጨፍለቅ ዘመቻ ይዟል። ተቃዋሚዎችን ለመከፋፈል የጀመረው ዘመቻ ከቅንጅት ውህደት ተቃውሞ ተነስቶ አጋር ተቃዋሚዎች እስከማፍራት ሄዷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ቫንኩቨር ሮቤልን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች Print E-mail

በሲያትል ኮንሰርቱን የሚያቀርበው ቴዲ አፍሮ ሮቤልን ቀበላል ተብሎ ይጠበቃል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 29 ቀን 2002 ዓ.ም. February 6, 2010)፦ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን በመወከል ለፈረንጆቹ የክረምት የበረዶ ላይ የስፖርት ውድድር ተሳታፊ የሆነው ሮቤል ተክለማሪያምን ለመቀበል ዝግጅቱ መጠናቀቁን በቨንኮቨር የሚገኘው ግብር ሀይል ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ኢትዮጵያዊው ሮቤል በቫንኩቨሩ የክረምት ኦሎምፒክ ይሳተፋል Print E-mail

Robel TeklemariamEthiopia Zare (ሐሙስ ጥር 20 ቀን 2002 ዓ.ም. January 28, 2010)፦ በክረምት ኦሎምፒክ ታሪክ ኢትዮጵያን ወክሎ በመወዳደር የመጀመሪያው የሆነው የ35 ዓመቱ ወጣት ሮቤል ተክለማርያም በሚቀጥለው ወር በቫንኩቨር - ካናዳ በሚጀመረው የክረምት (ዊንተር) ኦሎምፒክ ለመሳተፍ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የአየር መንገዱ አደጋ አጠያያቂ ሆኗል Print E-mail

ጥቁር ሳጥኑ ተገኘ

የሠራተኞች ስም ዝርዝር ይዘናል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ጥር 20 ቀን 2002 ዓ.ም. January 28, 2010)፦ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET-409 በተከሰተው አሰቃቂ አደጋ ከሞቱት 90 ሰዎች መካከል የ36ቱ አስከሬን የተገኘ ሲሆን፤ በበረራ ሥራ ላይ የተሰማሩት የአየር መንገዱ ሠራተኞች ማንነት መታወቁን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በሊባኖስ ተከሰከሰ Print E-mail

Ethiopian Airlines54 ሊባኖሳዊያንና 22 ኢትዮጵያዊያኖች ይገኙበታል

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 17 ቀን 2002 ዓ.ም. January 25, 2010)፦ከቤይሩት ወደ አዲስ አበባ ይበር የነበረ 737 ቦይንግ አውሮፕላን 90 የሚደርሱ ተሳፋሪዎችንና የአውሮፕላኑ ሠራተኞችን ይዞ ተከሰከሰ።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የተቃዋሚ አባላት እስራትና እንግልት ተባብሷል Print E-mail

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 8 ቀን 2002 ዓ.ም. January 16, 2010)፦ምርጫ 2002ን አስታኮ በየክልሉ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እስርና እንግልት እየተባባሰ መምጣቱን የየፓርቲዎቹ አመራሮች እየገለጹ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የፖለቲካ ድርጅቶች ክርክር ተጀመረ Print E-mail

መድረክ ውርስ ይገባኛል ሲል ኢህአዲግ አፈገፈገ

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥር 7 ቀን 2002 ዓ.ም. January 15, 2010)፦ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል “ምርጫና ሰብዓዊ መብቶች” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የመጀመሪያውን የፓርቲዎች ክርክር ጀመረ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

መድረክ አምስት ጣትን ለምልክት መረጠ Print E-mail

መድረክንና መኢአድን ያወዛገበው የአውራ ጣት ምልክት ለመኢአድ ተሰጠ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 1 ቀን 2002 ዓ.ም. January 9, 2010)፦ በአውራ ጣት የምርጫ ምልክት ውዝግብ ውስጥ በገቡት በመድረክ እና በመኢአድ መካከል ውሳኔ ያላገኘው መድረክ በምርጫ ቦርድ ትዕዛዝ አውራ ጣትን በአምስት ጣት እንዲቀይር ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የአንድነት አባላት ወደ መኢአድ እንዲቀየሩ እየተገደዱ ነው Print E-mail

“አንድነት ሊዘጋ ይችላል” ኢንጂ. ግዛቸው

Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 30 ቀን 2002 ዓ.ም. January 8, 2010)፦ በኢህአዲግ ካድሬዎች አስገዳጅነት በአማራ ክልል የሚገኙ የአንድነት አባላት ወደ መኢአድ እንዲቀየሩ እየተገደዱ መሆኑን ወደ አዲስ አበባ የገቡ የአንድነት አባላት ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በኢትዮጵያ ለውትድርና ጥሪ ቀረበ Print E-mail

Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 30 ቀን 2002 ዓ.ም. January 8, 2010)፦ በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ድርጅት በወትድርና ሙያ የሚሠማሩ መስፈርቶችን በማስቀመጥ የውትድርና ምልመላ ጥሪ አቀረበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 86
 
Banner