ዋና ገጽ
 

ግቡን የሳተ ቀስት! Print E-mail

‘ኢሕአፓ’ - አዲሱ የነጻ ፕሬስ ጠላት!?

ከአትክልት እና ጓደኞቹ

የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ላለፉት 20 ዓመታት በእሳት የተፈተኑ ቁርጠኞች ናቸው። እስርና እንግልቱን በተደጋጋሚ የወጡበት የወረዱበት ሸክም ነው።  በጠራራ ፀሀይ በወያኔ ጥይት የተገደሉትን መርሳት ይከብዳል። ህክምና ተነፍገው ዘብጥያ ውስጥ የሞቱትንም ማስታወስ እንዲሁ... ይሰቀጥጣል። ዛሬም ወፍራም ወፍራም ክስ ተለጥፎባቸው ቃሊቲ ውስጥ የሚጉላሉትንም ልብ ይሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በሱማሊያ የኢትዮጵያ ጦር ሰፈር በአጥፍቶ ጠፊዎች ተጠቃ! Print E-mail

አልሸባብ 10 ወታደሮች ገደልኩ ብሏል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2004 ዓ.ም. January 25, 2012)፦ በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ጠቅላይ ሰፈር ላይ የአልሸባብ አጥፍቶ ጠፊ በሚኒባስ ሙሉ የታጨቁ ቦምቦች ማፈንዳቱ ተዘገበ። በጥቃቱ 10 የኢትዮጵያ ወታደሮች መግደሉን አልሸባብ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አፈር ስሆን፤ ፌስ ቡክዎ ላይ አድ ያድርጉኝ! Print E-mail

አቤ ቶኪቻው

ውድ ጠቅላይ ሚኒስትር… ብዬ ልጀምር ነበር “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት!” ሲሉኝ ታየኝና ተውኩት።

ቆይ እስቲ ወዳጄ መጀመሪያ ከእርስዎ ጋር ሰላምታ እንለዋወጥ። እርስዎ ኖት ቀሪ ሃብቴ…! እንዴት አሉልኝ…? ጤናዎ አማን ነው? ግራ ቀኙ ሁሉ ሰላም ውሎ አድሯል? ጎሽ እንዲህ ነው እንጂ የጨዋ መልስ! እርሱ ጠባቂው ለወደፊቱም እቅፍ ድግፍ አድርጎ ይጠብቅልኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ምርኮኛ - ቅኝት መስፍን ማሞ ተሰማ (ሊያነቡት የሚገባ) Print E-mail

የመጸሐፉ ደራሲ ቆንጅት ብርሃን

መንደርደሪያ

ደምና ዕንባ ተቀላቅሎ በብዕር ሲቀሰም ምንን ይወልዳል? ምርኮኛ! ምርኮኛ የደም መፅሀፍ ነው።  የዕንባ መፅሀፍ። የአንድ ትውልድ ደም፤ የአንድ ትውልድ ዕንባ የተተረከበት የደም ዕንባ ታሪክ። ምርኮኛ አንባቢን ምርኮኛው አድርጎ በትርክቱ ባህር እየደፈቀ፤ ትንፋሽ እስኪያጥር ነፍስ እስክትቃትት አካልና መንፈስን ረግጦ የሚገዛ፤ ሃያል የደም ዕንባ ታሪክ ነው - ያልታደለው ትውልድ ታሪክ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በአፋር ክልል ለታገቱት ጀርመናዊያን አርዱፍ ኃላፊነት ወሰደ Print E-mail

‘5ቱ ጎብኝዎች የሞቱት በኢትዮጵያ መንግስት ጥይት ነው’ አርዱፍ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 14 ቀን 2004 ዓ.ም. January 23, 2011)፦ ባለፈው ሳምንት ለ5 ጎብኝዎች ሞት ምክንያት ለሆነው እና ለ27 ጎብኝዎች ላይ ለተቃጣው ጥቃት በህወሀት መራሹ የኢትዮጵያ ወታደሮችና በአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (አርዱፍ) መሀከል በተነሳ ጦርነት መሆኑንና ታጋቾቹ ሁለት ጀርመናዊያን በእጁ እንደሚገኙ አርዱፍ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ፖለቲካን መጋፈጥ እንጂ ማምለጥ አያዋጣም Print E-mail

ሉሉ ከበደ

የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነው። አንድ ቀን አባቱን ጠየቀው፤ ” አባባ ፖለቲካ ምንድነው?” “ ጥሩ ጥያቄ ነው ልጄ! ቁጭ በል በምሳሌ አስረዳሀለሁ። “ ይልና አባት ልጁን ካስቀመጠ በሗላ ‘’ፖለቲካ ማለት እንግዲህ ይህን ቤታችንን እንደ ሀገር ቁጠረው። ቤታችን ሀገር ማለት ነው። በቤታችን ውስጥ ስራ እየሰራሁ ገንዘብ የማመጣ እኔ ነኝ።  እኔን እንደ ካፒታሊዝም ቁጠረኝ። እኔ ካፒታሊዝም እባላለሁ። እናትህ ደግሞ እኔ በማመጣው ገንዘብ ለቤታችን የሚያስፈልገንን ሁሉ ምግብም ልብስም ሌላውንም እየገዛች ታስተዳድረናለች ማለት ነው። እናትህን ደግሞ እንደመንግስት ቁጠራት። እናትህ መንግስት ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የሁለት አምባዎች ወግ... ወግ አንድ - ናፍቆቴን መልስልኝ Print E-mail

ያሬድ ጥበቡ (የቀድሞ ኢህዴን / ብአዴን ሊቀመንበር ነበሩ)

የዘንድሮ የልደት በአል ከወትሮው ለየት ያለ ነበር። ገፀ በረከትም ነበረው፣ ያውም ሁለት። በረከት ስምኦንና ሌተና ኮሎኔል መንግስቱ ያቀረቡልን ሰጦታ። ስጦታዎቹንም ከከፈትሁ በሁዋላ እኔም ስለሁለቱ አምባዎች ወግ ላወጋችሁ አሰብኩ። አንዱ አምባ የኢህአዴግ መሆኑ ነው ሌላው ደግሞ የደርግ። አምባ ላይ የሚሸልል ደግሞ አምባገነን ነው። እናንተዬ ይህን ቃል የፈጠረ መንዜ የኖቤል ሽልማት እንደሚገባው አትስማሙም? የመጀመሪያውን ወግ ‹‹ናፍቆቴን መልስልኝ›› አሰኝቸዋለሁ። ያለምክንያት አይደለም። ከአንድ ሁለት አመት በፊት “አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ ላቀረበልኝ ቃለምልልስ ‹‹የአዲሱና በረከት ሳቃቸው ይናፍቀኛል›› ብዬ ናፍቆቴን በአደባባይ ገልጬ እንደነበር የጋዜጣዋ ታዳሚዎች ያስታውሱ ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የመለስ ቦላሌ! Print E-mail

ግርማ ደገፋ ገዳ

የመለስ ቦላሌ “ቦላሌ” ከመሆኑ በፊት ቁምጣ ነበር። አዲስ አበባ ለትምህርት ሲመጣ ቦላሌ ሆነ። ማገብት ጠርቶት ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ሲመለስ እንደገና ወደ ቁምጣ ተለወጠ። ዳግም ወደ ቁምጣ ሲቀየር፣ ሃሳቡ ኃይለኛ ቁምጣ ሆኖ ለመቅረት ነበር። ይሁንና አንዴ ቦላሌ አንዴ ቁምጣ እየሆነ፤ ራሱን እየቀያየረ በረሃ ከረመ። የሓርነት ድርጅቱ ተለዋጭ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል ደረጃም ደረሰ። ድርጅቱ በገንዘብ ጠብሽ በተቃጠለበት በአንድ ወቅት፣ የአድዋን ባንክ መዝረፍ አማረው። አምሮትም ዝም አላለም፤ ድርጅቱን ሚሊዮን በሚሊዮን የሚያደርጉ ዘራፊዎችን መረጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ከጓድ መንግስቱ ኃይለማርያም ‹‹ትግላችን›› ጋር… Print E-mail

ተመስገን ደሳለኝ

ማን ይፈራል ሞት

ማን ይፈራል

ለእናት ሀገር ሲባል..

የጊዜው ወታደራዊ ደርግ አስተዳደር፣ የአብዮታዊ ጦር ሰራዊት ጠቅላይ አዛዥ፣ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ ዋና ፀሀፊ፣ የኢህዴሪ ሊቀመንበር፣ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት… ጓድ መንግስቱ ኃ/ማርያም ሰሞኑን በስደት ከሚኖሩበት ዙምባቤ ‹‹ትግላችን›› የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመው በ39 የአሜሪካ ዶላር እየቸበቸቡ ነው። በእርግጥ ሀገር ከመሸጥ መጽሐፍ መሸጥ የተሻለ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

አሳዛኝ ዜና Print E-mail

በተስፋዬ ገብረአብ

ይህን አሳዛኝ ዜና የሰማሁት፣ ጥር 17፣ 2012 ተስያት ላይ ነበር። አንድ ጓደኛዬ በስልክ እንዲህ ሲል ጠየቀኝ፣ “ኢህአፓ የፈፀመውን ሰማህ?” “አልሰማሁም። ምን ፈፀመ?” ባጭሩ ነገረኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 126

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 


ኢሳትን ይርዱ!

Banner